Saturday, January 30, 2016

አስተርእዮ ለማርያም

በዓሉ አስተርእዮ መባሉ ግን ሁለት ነገርን ያሳያል አንድ ወራቱ ማለት ጥር ጌታችን በጥምቀቱ ምስጢረ ሥላልሴን ከዚያም ጋር አምላክነቱን ለዓለም የገለፀበት በመሆኑ ሲሆን ሁለተኛ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አምላክን በወለደችበት ስብሐተ መላእክትን በሰማችበትና ባየችበት የልደት ወራት  አካባቢ ከዚህ ዓለም በሞት ተለታ ወደ ሰማይ ስትወጣ በስማይም በምድርም ለሰውም ለመላእክትም  ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕርይ አባቱ አብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ የተሰጣት ጸጋና ክብር መገለጡን ያሳያል "አስተርእዮ" ማለት መታየት መገለጥ ማለት ነውና።የኢትዮዽያ ሊቃውንት በዚህ ቃል ሐሳባቸውን ያስተባብራሉ ቅዱስ ያረድ አምላክ ከድንግል በሥጋ መወለዱን በዚህም በአካለ መጠን ለዓለም መገለጡን አተርእዮ ብሎ ሲናገር ሌላው ደግሞ{ደራሲ ሊቅ }የትንቢት አበባ እግዚአብሔር የእኛ ሥጋ የሆነውን ያንቺን ሥጋ ለብሶ በምድር እንደተገለጠ ለእኛም እንደታወቀ ድንግል ሆይ የመገኛችን መመኪያ ዛሬ ለእናታችን ለማርያም በሰማይ በፍጹም ደስታ መገለጥ ሆነ እያልን እናመሰግንሻለን ብሏል።እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጥር 21 እሁድ ቀን በ49 ዓ.ም በ64 ዓመቷ አርፋ ከዚህ ዓለም ወደ ዘለዓለማዊ ህይወት በምትሸጋገርበት ዕለት{በዕረፍቷ ቀን} ቅዱሳን ሐዋርያት አስከሬኗን ወደ ጌተሴማኒ መቃብር በሚወስዱበት ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ከዚህ ቀደም ልጇን ኢየሱስን "ሞተ፣ ተነሳ፣ አረገ ደግሞ በክፉወችና በበጎወች ለመፍረድ ይመጣል" እያሉ ሲያውኩን ነበር። አሁን ደግሞ ይህችን እናቱን ዝም ብንል "ሞተች ተነሳች" እያሉ ሊያውኩን አይደል አሁንም "ኑ በእሳት እናቃጥላት" ብለው ከእነርሱ መካከል አንዱ ታውፋኒያ ወይም ሶፍንያስስ የሚባለውን ልከው አስከሬኗን ለማቃጠል የተጠቀሰው ሰው ተረማምዶ በድፍረት የአልጋውን ሸንኮር ሲጨብጥ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሁለት ትክሻው በሰይፍ ቀጣው። ሁለቱ እጆቹም ከአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ።ይህም ቅጣቱ ስላስደነገጠው በይበልጥም ምክር ስለሆነው ወዲያውኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ እርሷም ወላዲተ አምላክ መሆኗን አምኖ በልጇ ቸርነት በእርሷ አማልጅነት ተማምኖ ምህረትና ይቅርታን ስለለመነ በቅዱሳን ሐዋርያት ጸሎት በእመቤታችን አማላጅነት እጁጆቹ እንደነበሩ ተመልሰውልታል።ሥጋዋንም ቅዱሳን ሐዋርያት ለጊዜው ጌቴሴማኒ በተባለው ቦታ አሳርፈውታል በሶስተኛው ቀን ግን መላእክት ከዚያ አፍልሰው  በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑረውታል።ከመቃብር እስከተነሳችበት ዕለት ድረስ ለሁለት መቶ  አምስት ቀኖች በዚያው ቆይቷል።ክርስቶስ ለሚመጣበት ለ2500 ዓ.ም ምሳሌ ነው። 200 የ 2ሽህ 5ቱ የ500 በዚህ ጊዜ የሰው ሁሉ ትንሳኤ ይሆናል።በዕለተ እረፍቷ ብዙ ፍጹም በረከት ተሰጥቷል።የፈውስ ጸጋ ከደረሳቸው አንዱ ታውፋንያ ነው።በዚህ ዕለት የተደረገውን ሁሉ የታሪክ መጻህፍት ዘርዝረው ያስረዳሉ።በዚህ የተጠቀሰው ግን በአጭሩ ነው።ስለዚህ በእረፍቷ ምክንያት ጥር 21 ቀን የተጀመረው በዓል መታሰቢያ በየወሩበ 21 ቀን እንዲታሰብ የኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት ስለሆነ ወሩ በገባ በ21ቀን የእረፍቷ በ29 ቀንም አምላክን የመውለዷ መታሰቢያ ይከበራል።ይህም በቀድሞ መባቻ በዓል ፈንታ የገባ ነው። ያ ጥላ ምሳሌ ስለነበር አምናዊ ተተክቶበታል።

                                                                        ምንጭ፦መጽሐፈ ታሪክ ወግስ

No comments:

Post a Comment