Saturday, July 11, 2015

የፍጻሜ ልዑል

የፍጻሜ ልዑል
በገፍ እየጠጣ ወንዝ እና ዝናሙን ባህሩ ካልረካ፣
በጅምላ እያቀፈ ፀሐይ ከዋከብቱን ጠፈሩ ካልፈካ።
በቀረብነው ቁጥር ግባችን ከራቀ፣
የተጀመረ እንጅ ባይኖረን ያለቀ፣
ጣእመ ህላዌ እንዳይሆን መራራ፣
ቅስም እንዲያንሰራራ፣
መሃላችን ካለ
ባ'ለ ብዙ ጅምር ባለ ሺህ ሙከራ፣
የፍጻሜ ልዑል ተብሎ ይጠራ።
ምንቸት እና ጋን
ይኑር እንጅ ባ'ገር፣
በቀየ በሰፈር፣
ኩሬ ሙሉ ዉሃ ምድጃ ሙሉ እሳት
ዳውላ ሙሉ አፈር፤
የምንቸቶች ስፍር መች በጋን ይለካል፣
ጋኖች እንኳን ቢያልቁ ሌላ አፈር ይቦካል።

ምንጭ፦ ስብስብ ግጥሞች
                               በውቀቱ ስዩም