Saturday, April 30, 2016

አደናጋሪው ጩኸት !

መላዋ እየሩሳሌም የጩኸት ድምጽ ይሰማባታል፤ከወትሮዋ በተለየ ሁኔታ ጩኸት በዝቶባታል። ከወዲያ ወዲህ እየተመላለሱ ህዝቡን የሚያሳምፁ ካህናቱና ሊቃነ ካህናቱም ወገባቸውን ታጥቀው ይመላለሱባታል። የከተማዋን ሽብር የተመለከቱ ሁሉ  ገበያ ቀን ነበርና ግራ ተጋቡ በሚሰሙት ጩኸት ተደናገሩ፣የጩኸቱን ምክንያት ተረድቶ ማስርዳት የሚችል ግን አንድም ሰው የለም ብቻ ሁሉም ይጮሃል። በመንገድ አልፈው የሚሄዱትም "ቤተመቅደስን አፍርሰህ በሦስት ቀን የምተሰራው"  እያሉ ይጮሁ ነበር። ከቤተ መንግስትም ሆነ ከቤተ ክህነቱ ባለስጥናት  ጩኸቱን ለማስቆም  የደፈረ ማንም የለም። ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በተደረገው ተዓምራት በሕሙማን አድረው ይጮሁ የነበሩ አጋንንት ዛሬ ደግሞ በአይሁድ ልቡና አድረው ይጮሃሉ። ጩኸቱ ግን ይለያያል። ያን ጊዜ" ልታሳድደን መጣህን? "የሚል ሲሆን ዛሬ ግን "ስቀለው! ስቀለው!" የሚል ሆኗል። ነገሩ እየጠነከረ መጥቶ ጩኸቱ ምክንያት የሆነው ንጉሠ አይሁድ ኢየሱስ ክርስቶስ ታስሮ ወደ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ደርሰ። 


ሊቀ ካህናቱ ሀና ሥልጣን ዘመኑን ጨርሶ ለቀያፋ ያረከበ ቢሆንም ስለምግልናው በጀመሪያ በተከሳሹ ላይ ፍርድ እንዲሰጥ የተጠየቀው እርሱ ነበር። ነገር ግን እርሱም ቢሆን ጩኸቱ ለማስቆም አቅም አልነበረውም። ሲጀመርም ጩኸቱን መርቆ የከፈተው ማን ሆነና? የእርሱ የልጅ ባል ቀያፋ አይደለምን? "ስለ ህዝቡ ሁሉ አንድ ሰው ቢሞት ይሻላል" ብሎ። በዚህ በሊቃነ ካህናቱ የተጀምረው ጩኸ ወደ ሕዝቡ ወረደ በሊቀ ካህናቱ ግቢ የፍርድ ሂደቱ እየተካሄደ ባለበት ወቅት  ሌላ አዲስ ጩኸት ተከሰተ ፤የሰባኪው ዶሮ ጩኸት ተከሶ የመው  የክርስቶስ ፍርድ ሳይጠናቀቅ ደቀመዝሙሩ ዼጥሮስም ተከሶ ቆመ። በሕሊና ዳኝነት ወንጀለኛ መሆኑ ስለተረጋገጠ ምስክር እንኳን ሳያስፈልገው እራሱ በሰጠው የእምነት ቃል ማስረጃነት ዳኛው አስቸኳይ ውሳኔ ስለሰጡ ዼጥሮስ ስለራሱ እያለቀሰ ወ። ምንላባትም የኸቱ ምስጢር ገብቶት ስለራሱ ይጮህ የነበረ ብቸኛ ሰው ሳይሆን አይቀርም። ሌሊቱን በሙሉ አንድ ጊ እንኳን ሳይተኙ በጩኸት ከሐና ወደ ቀያፋ ከቀያፋም ወደ ሐና እያመላለሱት ሲጮሁ አደሩ። ሲነጋም የካህናት አለቆች ህዝቡ ሁሉ አሉ የትባሉትን ሽማሌዎች ጠርተው የሞቱን ጦማር አጸደቁት ። ከሳሽ ሳይኖር በደሉ ሳይዘረዘር  እንዲሞት የተወሰነበት የመጀመሪያ ሰው።

Tuesday, April 26, 2016

ሀቁን ካንቺ ልስማ

ሰላም ላንቺ ይሁን ለንጽህት እናቴ
ሳዝን መጽናኛየ ስደክም ብርታቴ፣
የመኖሬ ምስጢር የህይወቴ አንድምታ፣
ከሰማይ የተላክሽ የንጉሥ ስጦታ ፣
አማናዊት መርከብ ምሥለ ጎልጎታ፣
የሸክሜ ማቅለያ የምስጢር ዋሻዬ፣
ከጭንቀት ማምለጫ ጥላ ከለላዬ፣
ሰላም ላንቺ ይሁን ሰላም ነሽ እማዬ?
የምነግርሽ አለኝ ጆሮ ስጭኝ እማ!
እኒያ ጡት ነካሾች ሲሰድቡሽ ብሰማ፣
ውስጤ ተቃጠለ ሕሊናዬ ደማ፣
እውነቱን ንገሪኝ ሀቁን ካንቺ ልስማ፤
እውነቱን ንገሪኝ ሀቁን ካንቺ ልስማ።
ምን ጥፋት ሰርተሽ ነው? ምን በድለሻቸው?
አሻግረው ስላዩሽ ሚያንገሸግሻቸው።
ቆይ ምን ብተሰሪ ነው?
እኮ ምን ሰርተሽ ነው? ምንድን ነው ነገሩ?
እናጠፋታለን ብለው ሚፎክሩ።
ለምስጢር ያልበቃሁ ብሆንም ጎስቋላ፣
ትዕዛዝሽን ያልጠበቅሁ አደራ ምበላ፣
አፈር ትቢያም ብሆን ቢበዛም ሀጢአቴ፣
ቃላት መገጣጠም ባይችል አንደበቴ፣
እውነቱን ልወቀው ንገሪኝ እናቴ፤
እውነቱን ልወቀው ንገሪኝ እናቴ።