Tuesday, May 30, 2017

ወአንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም


“ወአንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም።እናንተ ግን ከሰማይ ኃይልን እስክትለብሱ ማለትም ሰማያዊ ሃብትን ሰማያዊ እውቀትን ገነዘብ እስከምታደርጉ ድረስ በኢየሩሳሌም ኑሩ ሉቃ፦24:49። ይህ ዶግማ ነው ወገን! ሰማያዊ ሃብት መንግስተ ሰማያትን ገንዘብ እስከምናደርግ ድረስ በኢየሩሳሌም(በቤተክርስቲያን ጥላ ስር) መቆዬት። የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ከሚወርድባት ከማርቆስ እናት ቤት አለመጥፋት።” ዲ/ን ጌታቸው ቢሰጠኝ። 

“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ማደሪያዎችህ እንደምን የተወደዱ ናቸው! ነፍሴ የእግዚአብሔርን አደባባዮች ትወድዳለች ትናፍቅማለች፤ ልቤም ሥጋዬም በሕያው አምላክ ደስ ተሰኘ።ወፍ ለእርስዋ ቤትን አገኘች፥ ዋኖስም ጫጩቶችዋን የምታኖርበት ቤት አገኘች፤ የሠራዊት አምላክ ንጉሤም አምላኬም ሆይ፥ እርሱ መሠዊያህ ነው። በቤትህ የሚኖሩ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፤ ለዓለምና ለዘላለምም ያመሰግኑሃል።አቤቱ፥ እርዳታው ከአንተ ዘንድ የሆነለት፥ በልቡም የላይኛውን መንገድ የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው።በልቅሶ ሸለቆ ውስጥ በወሰነው ስፍራ የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና።ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል። 

የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ ጸሎቴን ስማ፤ የያዕቆብ አምላክ ሆይ፥ አድምጥ።አቤቱ፥ መታመናችንን እይልን፥ ወደ ቀባኸውም ፊት ተመልከት።ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ።መዝ 83፦1-10።”

የ2009ዓ.ም የጅ/ዩ/ዋ/ግ/ግ/ጉ ምክክር ንዑስ ክፍል አባላት ከሻይ መርሃ ግብር መልስ በአለን ደብረገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ግንቦት 19/2009 ዓ.ም።

Monday, May 22, 2017

ግንቦት 11 ቅዱስ ያሬድ የተሰወረበት እለት

በዚች እለት የሱራፌል አምሳላቸው የሆነ ማህሌታዊ ቅዱስ ያሬድ የተሰወረበት እለት ነው፡፡ ይህም ቅዱስና ሊቅ አባቱ አዳም፥ እናቱ ታውክልያ ይባላሉ፡፡ያሬድ ማለት፦ሙራደ ቃል ማለት ሲሆን ብሔረ ሙላዱ ከዘርዓ ሌዋውያን አኩሱም ነው፡፡ የተወለደውም በ505 ዓ.ም ነው፡፡ ይኼም ቅዱስ ከገበዘ አኩሱም ከአባ ጌዴዎን ዘመዶች ወገን ሲሆን በኢትዮጵያ ከምትቀድመው ከአኩሱም ካህናት ውስጥ ነው፡፡አባ ጌዴዎን ከካህን አባቱ ከአዳም ተቀብሎ ትምህርትን ሊያስተምረው በጀመረ ጊዜ መቀበልና ማጥናት እስከ ሰባት ዓመት ድረስ ተሳነው፡፡ ባንዲት እለትም አባ ጌዴዎን በእርሱ ላይ ተበሳጭቶ ገርፎ አሳመመው፡፡ ያሬድም ሸሽቶ ወደቤተሰቦቹ ለመመለስ ከዱር ውስጥ ገባ፡፡ ከኀዘኑም ብዛት የተነሳ ከዛፍ ስር ተጠለለ፡፡ ከተጠለለበትም ዛፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመለከተ፡፡ ትሉም ከዛፉ እኩሌታ ደርሶ ይወድቅ ነበር፡፡ እንዲሁም ብዙ ጊዜ ከወጣና ከወረደ በኋላ በብዙ ጭንቅ ከዛፉ ላይ ወጥቶ ፍሬዋን ሲበላ ተመለከተ፡፡ እኔምኮ እንደትሉ ብዙ ብደክምና ብተጋ ሊገለጥልኝ ይችላል በማለት ተመልሶ መምህሩን አባ ጌዴዎንን፦አባቴ ይቅርታ አድርግልኝና እንደወደድህ አድርገኝ አለው፤ መምህሩም አባጌዴዎን በደስታ ተቀበለው፡፡

ከዚያም በኋላ እግዚአብሔር ኅሊናውን ንፁሕ፥ ልቡናውን ብሩህ አድርጎለት ባንዲት ቀን ብሉይና ሐዲስን ወስኖ ተገኝቷል፤ ዲቁናም ተሹሟል፡፡ በዚያም ወራት እንደዛሬው በከፍተኛ ቃል የመዝሙር ማኅሌት የለም ነበርና እግዚአብሔር መታሰቢያ ሊያቆምለት በወደደ ጊዜ ከኤዶም ገነት ሶስት አእዋፋትን ላከለት፡፡ እነሱም በሰው አንደበት ሲያነጋግሩት ተመስጦ መጣበት፡፡ ሶስቱም ወፎች ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ሀገር ወሰዱትና ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የሚያመሰግኑበትን ማኅሌታቸውን ተማረ፡፡ እግዚአብሔርም በመንበረ ጸባኦት ሆኖ በቃለ አቅርንት፥ በስብሐተ መላእክት ሲመሰገን ሰማ፡፡ወደ ምድርም በተመለሰ ጊዜ ጻጻሱና ንጉሱ፥ መሳፍንቱና ካህናቱ ለጸሎት ተሰብስበው ሳሉ ከጥዋቱ በሶስት ሰዓት በአኩሱም ወረደ ከመላእክትም የሰማውን በታላቅ ቃል፦ሃሌ ሉያ ለአብ፥ ሃሌ ሉያ ለወልድ፥ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለፅዮን ሰማየ ሳረረ፥ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ ብሎ አመስግኗል፡፡ ትርጉሙም፦ለአብ ምስጋና ይገባል፥ ለወልድ ምስጋና ይገባል ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፤ የፅዮንም ደገኛዋ ሰማይን ፈጠረ ዳግመኛም እንዴት እንደሚሰራት የድንኳኑን አሠራር ለሙሴ አሳየው አስተማረው ማለት ነው፡፡

Thursday, May 11, 2017

ለጽጌረዳ(Y.f)

ሰላምና ጤና ደስታና ፍቅር ምን ጊዜም ቢሆን ካንቺ አይለዩ። ከምንም ከማንም የማስቀድምሽ የምወድሽ የማፈቅርሽ እና የማከብርሽ  በልቤ ውስጥ ያነገስኩሽ ልዕልት ጓደኛዬ ለጤናሽ እንደምን አለሽልኝ። እኔ የፍቅር አምላክ የተመሰገን ይሁን እጅጉን ደህና ነኝ። ከሁሉም አስቀድሜ እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሰሽ ማለት እወዳለሁ። አሁን ከሌሊቱ 5:18 ሲሆን በግቢያችን የጌሾ ተሳፋሪዎች ድምጽ ምድርን እያንቀጠቀጣት ነው። አሮጌውን ዓመት ለማባረር ይሁን አዲሱን ለማስፈራራት አላውቅም ሰው ሁሉ ጥምብር እስከሚል ጠጥቶ እንደ አበደ ውሻ እየወደቀ እየተነሳ ይጮሃል ።እኔ ግን በናፍቆትሽ ብርታት እንጅ በተራ ነገር መስከር አላስመኘኝምና  እነሆ ልቤ እንደ ልደት ሻማ ቀልጣ  እንዳታልቅብኝ የሰጋሁ ይመስል ድንክ አልጋየ ላይ ተንበልብዬ ከማርና ከወተት በሚጣፍጠው ፍቅርሽ ሰከርኩልሽ።መነሳት እንጅ መውደቅ የሌለበት ጸጥታን የተጎናፀፈ የሀሴት ዝማሬ እንጅ ጩኸት የማይሰማበት ደስ የሚል ስካር! ፍቅር !ጽጌረዳዬ በዚህ ሰዓት ለበዓሉ ዝግጅት ሽርጉድ እያልሽ እንደሚሆን አልጠራጠርም።ፈጣሪ ፀሎቴን ቢሰማኝና የንሥር ክንፍ ቢሰጠኝ አንዴ ጀበናውን አንዴ ረከቦቱን ይዘሽ በሰፊው አዳራሽ ሰበር ሰካ  ስትይበት ማየት ብችል ምንኛ ደስ ባለኝ ።መብላት መጠጣት አልመኝም ነበር።አይ!አይ!እውነት ለመናገር በብራንጎድ የሚወረወር ከመሰለው ቡናሽ እፉት ካላልኩኝና የጉማሬ አለንጋ በመሰሉ ጣቶሽ ካላጎረስሽኝ በዓል ያከበርኩ አይመስለኝም። እማማ ትሙት! ሌላ ሰው ጥብስ ከሚጋብዘኝ መራራውን ጣፋጭ የሚያደርጉ እጆችሽ የነኩት ሽሮ ወጥሽን እመርጣለሁ፤ ኧረ እንዴው በበርበሬም ቢሆን።እኔ ምልሽ ውዴ አንቺንም እንደ እኔ አድርጎሽ ያውቃል?ናፍቆት፣ትዝታ፣ሰቀቀን፣ በቃ ምን ብዬ ልንገርሽ ?አሁን አሁንማ ደግሜ የማይሽ ሁላ አልመስልህ እያለኝ ተቸግሪያለሁ። የማያገኙትን ሰው መመኘት መጃጃል ቢሆንም እኔ ግን እንደ ንጋት ኮከብ የሚያበሩ ዓይኖችሽን፣ የውበት አምላክ በማይመረመር ጥበቡ አሳምሮ የደረደራቸው አበባ ጥርሶችሽን፣ የሃር ጉንጉን የመሰለ ፀጉርሽን፣እንደ ሚዳቋ ቀንድ የተቀሰሩ ጡቶችሽን እያየሁ፤ እንደ ዋሽንት የሚስረቀረቅ ድምጽሽን እየሰማሁ፤በደስታ ባህር መዋኘትና አውቆ መሞኘትን እመርጣለሁ። እናማ የኔ ውድ በፈቃዱ ያስተዋወቀን አምላክ ዳግም ያገናኘን ዘንድ የዘወትር ፀሎቴ ነው።እስከዚያው ድረስ ግን መልካም አዲስ ዓመት!

ምርኮኛሽ - ለ(Y.f)!ጳጉሜ 5/2008 ዓ.ም

Tuesday, May 09, 2017

እምሊባኖስ ንዒ

መዝገበ ርኅራኄ ድንግል ማርያም፣
ወልዳ የሰጠችን የዓለምን ሰላም፣
ለመላእክት እኅት እናት ናት ለዓለም።
ክብርት ናትና አምሳል የሌላት፣
ድንግል ተወለደች በመላክ ብስራት።
ድንግል ስትወለድ በአምላክ ቃልኪዳን፣
የሊባኖስ ጋራ ተሞላች በብርሃን።
ሀሴት አደረግን በፍጹም ደስታ፣
ምስጋናም አቀረብን ለአምላክ በዕልልታ።
የድንግል መወለድ ከእያቄም ከሐና፣
ስንጠብቀው የኖርን ተስፋችን ነውና።
ዘመድም ባታጣ ወዳጅ ቢኖራት፣
ሐና ምትወልድበት አልተገኘም ቤት፣
እንኳን ቤት በረቱን አይሁድ ነፍገዋት፣
በደብር ተወለደች የአምላክ እናት፤
አባቷ ሰሎሞን በቃለ ትንቢት ፣
ንዒ እምሊባኖስ እኅትዬ መርዓት ፣
ብሎ እንደዘመረ እንዳወደሳት።
ምንጭ ፦መዝገበ ታሪክ ክፍል አንድ

Sunday, May 07, 2017

ሰምታችኋል???


አልሰማንም እንዳትሉ! ያልሰማችሁ ስሙ! ይህ ትላንት ሚያዚያ 28 ቀን 2009 ዓ.ም የጅማ ዩኒቨርሲቲ  ዋና ግቢ ግቢ ጉባኤ 26ኛ ዓመት የምስረታ በዓልንና  የጅማ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቷ የከበረበትን 10ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ “ህይወት በግቢ ጉባኤ ቆይታና ከግቢ ውጪ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ የተላለፈ የመጨረሻው መልእክት ነው።

“እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ የእምነትን መጠን እንዳካፈለው፥ እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ እናገራለሁ።

በአንድ አካል ብዙ ብልቶች እንዳሉን፥ የብልቶቹም ሁሉ ሥራ አንድ እንዳይደለ፥ እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን፥ እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን። እንደ ተሰጠንም ጸጋ ልዩ ልዩ ስጦታ አለን፤ ትንቢት ቢሆን እንደ እምነታችን መጠን ትንቢት እንናገር፤ አገልግሎት ቢሆን በአገልግሎታችን እንትጋ፤ የሚያስተምርም ቢሆን በማስተማሩ ይትጋ፤  የሚመክርም ቢሆን በመምከሩ ይትጋ፤ የሚሰጥ በልግስና ይስጥ፤ የሚገዛ በትጋት ይግዛ፤ የሚምር በደስታ ይማር። ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን።

ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤  በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤ በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤  ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።  የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ። ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።  እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ፤ የትዕቢትን ነገር አታስቡ፥ ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ። ልባሞች የሆናችሁ አይምሰላችሁ። 

ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ።  ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።  ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና። ጠላችሁ ግን ቢራብ አብሉት፤ ቢጠማ አጠጡት፤ ይህን በማድረጋችሁ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራላችሁና።  ክፉውን በመልካም አሸንፉ እንጂ በክፉ አትሸነፉ። ሮሜ12፦1-21“

ይህንን መልዕክት ያስተላለፈው  ወንድማችን ዲያቆን ዳዊት እና ባለቤቱ ወይዘሮ የውብዳር በዚሁ ዕለት 10ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላቸውን በቦታው ተገኝተው በደስታና በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል። እኔም በቅናት መንፈሳዊ እርር ድብን ስል አመሻሽቼ እግዚአብሔር የመረጣቸው ፍቅሩና ስጦታው የበዛላቸው ጥንዶች ብያቸዋለሁ።
መልካም ዕለተ ሰንበት!!!

Saturday, May 06, 2017

amira's letter 3


DARLING PLEASE CONTACT THIS LAWYER FOR THE DOCUMENTS‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‏‎
My Sweetheart.

How are you doing over there together with your health? Hope fine and you are perfectly doing well in health. Thanks for your love and concern, Thank for your effort to help me over this topsy-turvey situation which am passing through since the abrupt death of my beloved parents, I am very grateful and I pray that Almighty will bless and empower you to achieve our goal. The message you acknowledge from the bank was also received & understood.


Firstly, I want you to comprehend, I love you from depth of my heart, I could kiss you a thousand times and still not be satisfied, My love for you is endless, so tender, so hot and complete. I swear to God I want you in my life. I love you more and more with each day passing and it eases me to know as tomorrow approaches, that I will love you more than yesterday and tomorrow will be more than today. My love for you cannot be measured by words alone as love does express my true feelings for you.


I thank God for you every day because I know you're heaven sent, you are my angel and I can't wait to join you as soon as we are through with this magnitude transaction. Darling, Please listen, I have never told anybody about this money the only person that knows about it is you and me no one again knows about it (since my parent's are dead).


Therefore, will advise you to keep it yourself due to am afraid of losing the money to people who will disappoint me when the money gets to there care, that is why it took me time to tell you about it and i promise you this from my heart (I AM NOT GOING TO DISAPPOINT YOU) and i equally expect the same from you.


Now,regarding the requests the bank needs from us i have with me here my late father statement of account (which i will give to the lawyer when he agrees to help us)and the death certificate,(which i will also give to him,so he can send them to you ) I thought it's the only thing the bank will need from us but since they need the power of attorney and the affidavit of support,i have informed the Reverend Pastor about it and he gave me the contact of this lawyer below, he is a registered lawyer in the United Nation Camp here and he is also a registered member in (Senegalese Bar Association) who will help in preparing the documents for us.
Please i will like you to contact him through email and phone today please to let him know how serious we are, When contacting him, tell him you are my foreign partner and you want him to prepare a power of attorney and also get the affidavit of Oath from high court here in Dakar Senegal and that he will do it in your name to enable the transfer of my (Late) father's Islamic Bank of Britain to your account.

Wednesday, May 03, 2017

letter from THE ISLAMIC BANK OF BRITAIN P.L.C


Welcome To The Islamic Bank of Britain P.l.c United Kingdom.
  

Islamic Bank

ISLAMIC BANK OF BRITAIN PLC 
HEAD OFFICE: Islamic Bank of Britain PLC, Birmingham B16 6AQ.  FREE POT: PO BOX 12461
(
islamicbank@onlinbanking.co.uk)
TEL: +
 447-866-075-778. Fax+44-703-194-1849
Date: March/27/2017.
FOR YOUR KIND ATTENTION.
Sir\Mr.Getaneh Kassie.
I have been directed by the director of Foreign Operation/Wire Transfer to write you in respect of your e-mail received. Actually we have earlier been told about you by the young lady Miss. AmiraIbrahim Fred that she wishes you to be her trustee/representative for the claim her late father's deposit with our bank.Late Dr Ibrahim Fred is our late customer with account no.BLB745008901546/QB/91/A substantial amount(US$7,400,000.00) of deposit with us. Hence you have been really appointed as a trustee to represent the next of Kin. However before our bank will transact any business concerning the transfer of the fund with you, we will like you to send the followings:

1. Power of Attorney and Affidavit of Oath permitting you to claim and transfer the funds to your bank account on her behalf. Note: This Power of attorney must be endorsed by a Senegalese resident lawyer (since the money is originated from Africa and the girl is currently residing in Senegal).

2. The death certificate of late Dr 
 Fred Ibrahim  (Her deceased father) confirming the death.

3. A copy of Statement of the account issued to Dr Ibrahim 
Fred by our bank.
Note that the above are compulsory, and are needed to protect our interest,yours, the next of kin after the claims. These shall also ensure that a smooth, quick and successful transfer of the fund will be make within 48 hours at reception of these documents.

Also you have to send your account information which will facilitate this fund as soon as these documents are been provided.Therefore You have to hurry up to present these documents to our bank to enable us wire the fund ( US$7,400,000.00 ) into your account. We promise to give our customers the best of our services. Should you have any question(s) please contact foreign transfer officer Mr 
Robert Owen on telephone number +447866075778 / fax +44-703-194-1849 for more directives /clarifications.

Yours Faithfully,
Mr Robert Owen. 
Foreign Operation International Transfer and Remittance  (I.B.B)

this letter was forwarded to amira like this,
Hi amira how are you doing today? I hope every thing is fine. here is the email from the islamic bank of britain sent in response to my requiest .as I told you before I am very happy to be with you all the time.what can  I do now please? never keep silent I am looking for your voice.yoursGetaneh Kassie