Tuesday, January 12, 2016

ጣፋጭ ፍሬን ላፍራ

የልቤን ቋጠሮ ቂም በቀል አንስተህ፣
ክፋት ምቀኝነት ቁጡነቴን ፍቀህ፣
መራሩን አንደበት በጣፋጭ ለውጠህ፣
ቀና ሰው እንድሆን ይጎብኘኝ መንፈስህ።
ቁጥቋጦ ቋጥኙ ይመንጠር ይወገድ፣
ሸክፈው ምላሴ በቃልህ ይሞረድ፣
ጉልበቴ ይንበርከክ ሰውነቴም ይራድ፣
መንፈስህ ይኑረው በልቤውስጥ መንገድ።
ቀዳዳው ተደፍኖ  ጎድጓዳው ይሞላ፣
ትዕቢትን ይናቀው ጥልቻንም ይጥላ
ትሕትናን በመልበስ ጥል ከእሱ ይከላ፣
መቅደስህ እንዲሆን መላው የእኔ ገላ።
ሕሌናዬ ሁሉ በጎ ነገር ያውጣ፣
በፊትህ የሚኖር ከህግህ ያልወጣ።
መልካም መሬት ይሁን የልቦናየ እርሻ፣
ጥፋጭ ፍሬን ላፍራ እስከመጨረሻ።


                      ምንጭ ፦ሐመር ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነሐሴ 2004ዓ.ም

No comments:

Post a Comment