Tuesday, February 02, 2016

ብላቴናው አይዞኝ

ፊቱን ቢያዞርብህ ሙድ ቢይዝ ዘመኑ፣
ብላቴናው አይዞኝ ያልፋል ሰቀቀኑ።
በርታ ጠንክር የሚል ባይኖርም ከጎኔ ፣
ሁለት  ሃብታት አሉኝ ችግር እና ወኔ።
ለአቡነ ተክሌ ክንፍ ለያዕቆብ መንሰላል፣
አይሳነው ልዑል  ሁሉንም ያድላል ።
ለ'ኔም በዝቶልኛል ጸጋ በረከቱ፣
ቢያድለኝ ቢያድለኝ ባይረካ ስሜቱ፣
ወኔን ደረበልኝ ማጣትን በብርቱ።
           
                        ጌታነህ  ካሴ

No comments:

Post a Comment