Saturday, February 20, 2016

ትላንትና ዛሬ

ትላንት እንደቆሸሽኩ ዛሬም አላታጥብኩም፣
በንጽሕ ሰው አምሳል ሰው መሆን አልቻልኩም፣
የራሴን ሳሙና ከመሸጥ አልዳንኩም።
ትላንት በደለኛ ትላንት አረመኔ፣
አምና በሲዖል ውስጥ ዛሬም በኩነኔ፣
ቁሞ የወደቀ ማነው ልክ እንደ እኔ?
የበደሉ ቅርጫት የክፉ ሰው ጓዳ፣
ሰውን ቁሞ ወቃሽ የኃጢአት ባልዕዳ፤
የፈርሰ ጎጆ ዝናብ የሄደበት፣
ለመቆም ያልቻለ ጊዜው ያለፈበት።
ከዓመት ዓመት ሲበር በኃጢአት በወሬ፣
በሰው ላይ ስቀልድ እየኖርሁ አብሬ፣
ስላልሰራሁበት በንስሐ አድሬ፣
ትርጉም የላቸውም ትላንትና ዛሬ።
 

 

 

                  ምንጭ፦ ሐመር መጽሔት
                            ኅዳር 2006 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment