Wednesday, April 17, 2019

...እርግማን...

ከዘመናት በፊት ያኔ ድሮ ድሮ
ሰው መሞት ሳይጀምር በቁሙ ተቀብሮ
መናኝ በሚያስቱ አስማታም  ጥርሶችሽ
ቀልብን በሚያሣጡ ምትሃተኛ ዓይኖች
እንኳን ሁለት ስንኝ እንኳን ስምንት ቀለም
ህይወት ብታስከፍይ ላንቺ ብዙ አይደለም
ብሎ የፃፈልሽ ጥቁር ቀለም ብዕሬ ዛሬ ተፀፅቷል
የሚመጥንሽን በረከተ መርገምት ግጥም አዘጋጅቷል
.
መልካም  ስመኝልሽ ሞት የደገስሽልኝ  አስመሳይ ወዳጄ
የስራሽን ዓይቶ  አምላክ  ይስጥሸ   እንጅ አትጠበቂ ከእጄ
እንኳን ሰውን ከሰው ከመላክ የጣላል ብለሽ የምትሰብኪ
ወንዝ ለማያሻግር ቅቤ ጠባሽ ምላስ ምትንበረከኪ
በመከራዬ  ቋት በጭንቀቴ ቁና ደስታሽን ምትለኪ
ከልብ የመነጨ በእንባ የታጠረ እርግማኔን እንኪ
.
ደስታ አልቮ መሆኔ ሲጨንቅሽ ሲከፋሽ
ክፉ ሰው  ካረገኝ እጀን አመድ አፋሽ
የተመኘሽ  ሁሉ በዬ ቦታው ይድፋሽ
ሚስት ከባል ያፋታል ብለሽ ምታስወሪ
የአሉቧልታ እመቤት የተንኮል  መሰሪ
የሰው ስም ለማጥፋት ነገር ምትቀምሪ
ወርቅ ለሰፈረልሽ ጉድጓድ ምትቆፍሪ
ቆመሽ እንደ ቀረሽ ለዘላለም ኑሪ
.
ከውኃ የጠራሁ ንፁህ ሰው መሆኔን ልብህ እያወቀ
እውነቱን የካደ አድር ባይ ህሊናህ  ውጊያ የሸመቀ
ሚስቴን ሊወስዳት ነው ብለህ ምታነባ
ወጥመድ አዘጋጅተህ ቦታ ምታመቻች  ቀን የምታደባ
ከዛች ነገር ፈታይ የጭን  ገረድህ ጋር እንጦረጦስ ግባ
.
04/07/11ዓ.ም
ዝቋላ ሆስፒታል 

No comments:

Post a Comment