Wednesday, April 17, 2019

....ያልሆኑም አሉና....

ለአንዱ በር ሲከፈት ለአንዱ እዬተዘጋ
ቀኑ የጨለመ ቢመስል የማይነጋ
አንተ መሬት ወድቀህ ዙፋን ላይ ቢወጡ
ጥሙ ሲያቃጥልህ ወይን ጠጅ ቢጠጡ
ከሌለው ላይ ወስደው ላለው ቢጨምሩ
ጎጆህን አፍረሰው ቪላ ቤት ቢሰሩ
እንጀራህ ቢቀጥን ከቅጠል ቢሳሳ
ሽርሽር ቢጥራሩ ነፍስያህ አልቅሳ
የቤትህ መቃጠል ቢሆናቸው ደስታ
በሲቃህ ስታይል ቢመቱም እስክስታ
ጊዜው የጣለህን እስኪያነሳህ ቀኑ
ፍጹም ተስፈ አትቁረጥ ያልፋል ሰቀቀኑ
መውጣትና መውረድ ቢበዛው መንገዱ
'ሺህ' ዎች ሲሸለሙ እልፎች ቢዋረዱ
አንተን መሆን ናፍቀው ያልሆኑም አሉና
ከአንደበትህ ይፈሰስ ይንቆሮቆር ምስጋና

ዶ/ር ጌታነህ ካሴ(ጌች ቀጭኑ) : ባህር ዳር(ፈለገሕይወት ሆስፒታል የጥርስ ህክምና ክፍል ውስጥ) ጥር 03 ቀን 2011 ዓ.ም ከቀኑ 9:00ላይ ተፃፈ።

No comments:

Post a Comment