Thursday, July 18, 2019

....አንተ ማለት....

በኦነግ ሸማ እቃ  ኩታህ ተሸምኖ
በህውሓት አርማ ገላህ ተጀቡኖ
አንተ ማለት አብን አንተ ማለት ማለት ፋኖ
መላሾ እያሳዬ ያሻው የሚነዳህ
ግጦሽ ስትከተል ህሊናህ የከዳህ
የግሌ ምትለው እውነት የለህ አቋም
ትላንት በጌታ ስም ዛሬ ደግሞ አቋቋም
ጥዋት ቤተመቀድስ ከሰዓት ቃልቻ
አርሴማን  ከዙቤር አስረህ በጋብቻ
እምነት ምናባቱ ገንዘብ ያስገኝ ብቻ
ዶግማ ገደል ይግባ  ይቀንቅን ቀኖና
አንተ ማለት ሳንቲም አንተ ማለት ዝና
በአብ ስም ጀምረህ በአላህ የምትጨርስ ሲራራ ነጋዴ
እንደ ልመና እህል የተደባለቀው ምርትህ ተቸርችሮ አላለቀም እንዴ?

 ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማን ነው?  አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ድቃቂ ሳንቲምና ዝናን ፍለጋ እዛም ቤት እዚህም ቤት ለምትልከሰከሱ ባተሌዎች! መልካም እለተ ሰንበት

07/11/2011 ዓ.ም
ዝቋላ ሆስፒታል 

Tuesday, July 09, 2019

...ሂፖክራቲክ ኦዝ...

የአባታችን ትዕዛዝ የቃል ኪዳኑ ቃል
በአንክሮ ላጤነው ምስጢሩ ይደንቃል
ከትእዛዛቱ ውስጥ አንደኛው ያይላል
መርዳት ባትችል እንኳ ሰው አትጉዳ ይላል
እናም ይህ መኃላ
ሂፖክራቲክ ኦዝ ሲመነዘር ቃሉ
አንድምታው ሲፈታ ሲራቀቅ ወንጌሉ
አንድም*
ከነፍሰጡር ሞት ጋር ዓይንህ አይላመድ
በሀጥአኑ መንገድ  እግርህ አይራመድ
ፈውስ ሆነህ ተፈጥረህ ከመርዝ አትዛመድ
አንድም*
መሪዎች ለገንዘብ ለሹመት አድልተው
መድኃኒት የሌለው ባዶ ቤት ገንብተው
ውኃና መብራቱን ድራሹን አጥፍተው
የጤና ሽፈኑን ምንትስ  አድርሰናል ብለው ሲሸልሉ
በሥልጣን መከታ በልዝብ አንደበት ህዝብን ሲያታልሉ
 በድብቅ መሳሪያ ታካሚን በሴራ በተንኮል ሲገድሉ
ትውልድ ከሚያመክኑ ነፍሰ ገዳዮች ጋር አትሸርብ ሴራ
እንቢ ለታካሚ ብለህ ተንጎራደድ ፎክርና አቅራራ
ታሪክ የማይረሳው ትልቅ ጀብዱ ስራ
የሚል ይመስለኛል
ይህን የሰሙ ግን ኢቲክሱን ጥሰሃህል እያሉ ያሙኛል
ተላልፈንም እንደሁ
በደሙ እያማገች በላቡ ቀቅላ
ሀገር እንደ ድመት ውድ ልጇን ስትበላ
 በደል ልኩን ሲያልፍ ግድቡ ሲሞላ
 ህገ-አምላክ  ይጣሳል እንኳንስ መኃላ

30/09/2011ዓ.ም
ዝቋላ ሆስፒታል

መልሱን ደብቅበት

አንደኛዬ ሆይ አንተ የአድባር  ዋርካ 
ድንጋይ ተንተርሰህ የከረምህ  በጫካ
.
ከሰውነት ወጥተህ መፅሐፍ ውስጥ የባጀህ
ለነገዋ  ተስፋ  ለዓላማህ መሳካትጊዜህን  የፈጀህ
የእሣትነት እድሜ ወጣትነትህን በንባብ የዋጀህ
አልጋና መከዳ ሲያማርጥ የኖረ ፀጉሩን እየቋጨ
ለንባብ  ስትወጣ መንገድ  የዘጋብህ ውኃ እየተራጨ
.
የአንደኛው መልስ ማነው ቢልህ በሹክሹክታ
ሰማሁህ አትበለው አትሁነው መከታ
መልሱን ደብቅና የእጁን ዋጋ ስጠው
የውድቀቱን ፅዋ ዛሬ ይጨልጠው
ልመናው በልጦብህ ምክሬን ብትል ችላ
እመነኝ ወዳጄ ለእኔ የደረሰው ይደርስሃል ኋላ
.
ስድስት ዓመት ተኩል ካሞፓስ ተቀቅዬ
ስመኝ የኖርኩትን ማዕረግ ተቀብዬ
ህዝቤን ለማገልገል ሠፈሬ ብመጣ
 በአቋራጭ ጎዳና ስልጣን ላይ የወጣ
ኮራጄ ጠበቀኝ ወንበር  ላይ ፊጥ ብሎ
የልጅነት ፍቅሬን መንትያ አሣዝሎአሣዝሎ

 05/10/2011 ዓ.ም
ዝቋላ ሆስፒታል