Tuesday, July 09, 2019

መልሱን ደብቅበት

አንደኛዬ ሆይ አንተ የአድባር  ዋርካ 
ድንጋይ ተንተርሰህ የከረምህ  በጫካ
.
ከሰውነት ወጥተህ መፅሐፍ ውስጥ የባጀህ
ለነገዋ  ተስፋ  ለዓላማህ መሳካትጊዜህን  የፈጀህ
የእሣትነት እድሜ ወጣትነትህን በንባብ የዋጀህ
አልጋና መከዳ ሲያማርጥ የኖረ ፀጉሩን እየቋጨ
ለንባብ  ስትወጣ መንገድ  የዘጋብህ ውኃ እየተራጨ
.
የአንደኛው መልስ ማነው ቢልህ በሹክሹክታ
ሰማሁህ አትበለው አትሁነው መከታ
መልሱን ደብቅና የእጁን ዋጋ ስጠው
የውድቀቱን ፅዋ ዛሬ ይጨልጠው
ልመናው በልጦብህ ምክሬን ብትል ችላ
እመነኝ ወዳጄ ለእኔ የደረሰው ይደርስሃል ኋላ
.
ስድስት ዓመት ተኩል ካሞፓስ ተቀቅዬ
ስመኝ የኖርኩትን ማዕረግ ተቀብዬ
ህዝቤን ለማገልገል ሠፈሬ ብመጣ
 በአቋራጭ ጎዳና ስልጣን ላይ የወጣ
ኮራጄ ጠበቀኝ ወንበር  ላይ ፊጥ ብሎ
የልጅነት ፍቅሬን መንትያ አሣዝሎአሣዝሎ

 05/10/2011 ዓ.ም
ዝቋላ ሆስፒታል

No comments:

Post a Comment