Saturday, May 12, 2018

ያማል 3

እና እደነገርሁሽ
የረዚደንት ቁጣ አይቶ መሳቀቁ
ሲኔር መጣ አልመጣ ሰውነት ማለቁ
ፖርተር ማፈላለግ ከነርስ መዳረቁ
ዱቲ አድሮ ለሞርኒንግ ሽር ጉድ ማለቱ X ray ማስነሳት BF ማሰራቱ የወለደች እናት ጫማ መፈለጉ ሞቶ የወጣን ፅንስ "alive" ማድረጉ
ያለ ዲሰፖዜብል ቪጎ ማስተካከል ካቴተር መንቀሉ የደሞዝ ቅናሹን አምኖ መቀበሉ ምን ብዬ ልንገርሽ ያማል ይሄ ሁሉ ታማሚ አስታሚ ወላጅ አስወላጁ አጥማቂ ሰቫኪው አስቀዳሽ ሰጋጁ የፈቃድ ባርነት በአንድነት ሲያውጁ ጨካኝ በበዛባት በዚች የምጥ ዓለም
ከዚህ የበለጠ ሌላ ህመም የለም
ጌች ቀጭኑ ዘታችቤት 02/09/10

ጭቅጭቁ ያማል
ንትርኩ ያማል
በዚህ ሁሉ  መሃል
ምርኮኛሽ  ጧት ማታ ከደጅሽ ይቆማል
በርሽ  ተንበርክኮ  ብሶቱን  ያሰማል
የሠናፍጭ ቅንጣት በምታክል እምነቱ  ተራራው ይገፋል
የማያልፍ ቀን የለም የጭንቁም ቀን ያልፋል
ይሄን ጊዜ ታዲያ
የማረክሽው ልቤ እርጥብ በሚያቃጥል የፍቅርሽ ነበልባል
ፀጉሩ ያላረረ የእንባ መስዋዕትን ለክብርሽ  ያቀርባል
እና እንደነገርሁሽ እኔ አንችን ስወድሽ
ይኸን ሁሉ ችዬ ነው የምላመድሽ
እና እንደነገርሁሽ
የ“quali” ማዕበል  ወጀቡ ቢንጠኝ
ዓመት ሙሉ አንብቤ grade C ቢሰጠኝ
ችግር ቢደራረብ መከራ ቢበዛ
ማርክ በዳሌ ቢሆን  በከንፈር ቢገዛ
እኔ አንችን ስወድሽ
ይሄን ሁሉ ችዬ ነው የምሳደድሽ
ኦ እናት medicine ፀሊም ወፀዓዳ
ጽዋሽ የማያልቀው ቢቀዳ ቢቀዳ
መዛመድ ሳያንስሽ ተግባርሽ የባዕዳ
ከጦርነት ማግስት ቦምብሽ ሚፈነዳ
ኦ እናት medicine እናት ህክምና
ይሻልሻል ብዬ ከአምና ከታቻምና
ወጣት ልጅነቴን
ክብር ማንነቴን
ቆንጥሬ ሳላስቀር ጠቅልዬ ሰጥቸሽ 
ገዝግዘሽ ገዝግዘሽ ቆርጠሽኝ ሰለቸሽ
ኦ እናት medicine ፀሊም ወፀዓዳ
መዛመድ ሳያንሰን ተግባርሽ የባዕዳ
የዓርነቴ ፀሐይ የነፃነቴ ጎህ እያልሁሽ ስመካ
ፍቅርሽ አሲምፕቶት የሚጠጉት እንጅ በዕጅ የማይነካ
ጎጻጉጽሽ ብዙ ቢሆን  በዚች  ዓለም
እኔ አንችን  ከመውደድ የሚያግድ አይደለም

Tuesday, May 08, 2018

ተፈስሒ በሏት

ፀሐይን  የምትወልድ ውብ ደማቅ ጨረቃ፣
ቀድመው ያኸለሟት ቴክታና ጴጥርቃ፤
እናትና ገረድ ድንግልና ሰማይ፣
ሐመልማልና እሣት ሐርና ወርቅ ፈታይ፤
መሰረታቲሃ ውስተ አድባር  ውእቱ፣
ብሎ ያወደሳት ዳዊት በትንቢቱ፣
ተወልዳለችና የአምላክ እናቱ፣
ከበሮ ይመታ ይድመቅ ማኅሌቱ።
ጠላት ኃይሉን ይጣ ይንቀጥቀጥ ዓለሙ፣
የሕርያቆስ  ልጆች ድምፃችሁን አሰሙ፣
ተፈስሒ በሏት ካህናት አዚሙ።
ትንቢት  ተፈፅሟል ያስተጋባ ቃሉ፣
ተወልደ ብዕሲ በውስቴታ በሉ።
ጌች ቀጭኑ ዘታችቤት ግንቦት 1/2010 ዓ.

በለቅሶ  ሚዘሩ በደስታ  ያጭዳሉ፣
ብሎን  ነበር  ንጉሥ በማይሻር  ቃሉ፤
እንባችን  ፍሬ አጣ ዋይታችን መከነ ፣
ምነው  በኛ ዘመን ትንቢት  ቅዠት ሆነ?

ከተኩላዎች መሃል

በንፁህ  መነጽር ማስተዋል ለቻለ፣
ለአቤል  መስዋዕትነት  ቢላው  የተሳለ፣
ከተኩላዎች መሃል ንጹህ  በግም አለ።
እርም አርጎ ትቶ ጥንብን  ለጥንብ አንሳ፣
ወደ ላይ ለመምጠቅ ክንፉን የሚያነሳ፤
ብቻውን  የሚኖር በጆፌዎች መንደር፣
ለአመነበት ጉዳይ የማይደራደር፤
ስለ ድንቅ ብቃቱ  ብዙም ያልተባለ፣
በቁራዎች ሰፈር ነጭ ንሥር አለ።
ይውጠው  ይመስል  ድንቁርናን ቁጣ፣
አባት ለገደለው የልጅ ልጅ ሲቀጣ፤
ቀድሞ ሰው መሆኑን አውቆ የተረዳ፣
ታናናሾቹ  ላይ  ደርሶ   ማይፈነዳ፤
አውቆ ለማሳወቅ ሁሌም  የሚተጋ፣
በጎሜ በነገር  ሰውን  የማይወጋ፣
ከእግዜር  የተቸረ በፀጋ ላይ ፀጋ፤
ስሜትን  የሚያድስ የጥርሱ  ፈገግታ፣
ሰው  አየሁ  በህልሜ ትላንትና   ማታ።
ገጾች  ስገለብጥ  በህልሜ  መዳፍ ላይ፣
እንደዚህ የሚል  ቃል ይነበባል  ከላይ፤
እንደ ሣተኖቹ አንተም ሁን  ሣተና፣
እኩል  የፈጠረህ  የአዳም  ዘር  ነህና።

Ped OPD ይካቲ 17/2010 ዓ.ም ከሌሊቱ 7:30 ተፃፈ