Sunday, March 27, 2016

አንደበት እና ጾም !

የተከበርክ ምላሴ ሆይ፡አርምሞን ገንዘብ አድርግ።አንተም ብዕረ አርምሞ የሚል ቃልን ጽፈህ ልቦናየን ለሚያውከው  ለዓይኔ መልእክት እንዲደርሰው አድርግ።ሥጋየ ፈቃድ በተነሳበት ጊዜ የጌታየን፣የፈጣሪዬን መከራውንና ግርፋቱን አስብ ዘንድ  ልቦናየ ይህን እያሰበ  እንዲበረታ እንዲህ ከሆነ ለዓለማዊ ህይዎት ሙት እሆናለሁ።ሣጋዊ ምኞትና ፍላጎት በነገሰበት ሕይዎት ለ አርባ አቅናት እንደ ጌታ ት ዝዛና ሕግ ልቡናዬን በንጽህና ለመጠበቅ ይቅርታ ለሚያሰጠው ህይዎት የተገባሁ እንድሆን።የ አባቶችን ምክር እቀበላለሁ፣የቅዱሳንን ፍኖት እከተላለሁ በከንፈሮቼ ላይ መዝጊያን አኑር ምክን ያቱም ብዙ መማር ስለሚገባኝ ነው  የምናገራቸውን ቃላርት እመጥን፣ሰውነቴን ለመቆጣጠር እችል ዘንድ፤ አንደበት የነስን ሩጫ ያሳድፋልና ሞገደኛ በሆነ የጻለ ሾተል ሰዎችን የሚገድል ሰው በቀላሉ ትንሽ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ያንበረክካል።ክንፍ ያላትን ከወጋች የንማትነቀለውን የምላስ ጦር የወረወረ ሰው(በ አላማም ያለ አላማም)አላማውን አይስትም።የቀረቡትን ሁሉ ያቆስላል ፤የመረዘውን ሁሉ ይገድላል።በጾም ወራት ሕሌና ፍጹም መረጋጋት ያስፈልገዋል።ከምድራዊ ሃሳቦች ሁሉ የጸዳ ከሰዎች ተለይቶ ብቻውን ከ አምላኩ ጋር የሆነ ሊሆን ይገባል።ሕሊና የኃዘን ደመና ሊያንዣብብበት ይገበዋል። ውጤቱም እርጥበት እንባን የሚያስከትል መራር ኃዘን ነው።


 ታላላቅ ነገሮችን ለመቆጣጠር የሚፈልግ ሰው ትንንሽ ነገሮችን መቆጣጠር ይኖርበታል። የምላሴን ኃይል ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር  ያለብኝ ከንፈሮቸ ምንም አይነት ቃላት እንዳያፈሱ ተስፋ አድርጌ  ለሰው ልጆች መርዙ የማይነቀል ገደይ እንደ ምላስ ያለ የለምና ነው። ምላስ ዘወትር ግልቢያን እንደሚናፍቅ  ከፊት ለፊት ያለውን ሁሉ ቀድሞ ለማለፍ እንደ ሚጋልብ ፈረስ ነው። ምላስ የተዘጋጀ የተደገነ ቀስት ነው። ሁሉን ማየት የሚቻለው ማን ነው? እጅ በአቅራቢያ የሚገኘውን ትንሽ ነገር በቀላሉ ይጨብጣል ፤እግርም ሁሉንም የመሬት ክፍል አይረግጥም፤አይንም ሰሜንና ደቡብን አይመለከትም፤ምላስ ግን የማይደርስበት ቦታ የለም። ምድርን ሁሉ ያካልላል ለነፍሰ ገዳዮችና ጣኦትን ለሚያመልኩ፣ሐሰትን ለሚዎወዱ አድጋ ነው በእብደታቸው ላይ ሌላ እብደት ይጨምርላቸዋልና። የፈጠነን ምላስ ሊያስቆም የሚችል ምድራዊ ኃይል የለም። ለመናገር የቸኮለ ከንፈርንም እንዲሁ ሰውም ቢሆን ውሽንፍርም ቢሆን፣የበረዶ ግግርም ጎርፍም፣ተራራም ቢሆን ባለ ቀስቱ ቅርብ ነው። ቀስቱ የተደገነ ነው፤ቀስቱ በደጋን ላይ ነው። አንድ ጣቱን ደጋን ላይ አድርጎ  አክሮ ቀስቱን ይወረውራል፤በረው የታለመላቸውን አላማ ይመታሉ። ሰማያዊያን ምድራዊያንም ቢሆኑ አያመልጧቸውም። ሕያዋንንም ሙታንንም ያለፉትን የሚኖሩትንና የሚመጡትን ሁሉ ይገድላል። የምላስ ቀስት እንዳይወረወርባቸው የሚጥብቁትንም የማይጠብቁትንም የተጣላቸውንም ወዳጆቹንም አይምርም።

Wednesday, March 16, 2016

አቤት ቆሻሻ !

በሀገራችን የዘመን አቆጣጠር ከ1980ዎቹ አጋማሽ አስከ1990 ዎቹ አጋማሽ ድረስ አልፎ አልፎ አዲስ አበባ ስታዲየም መግባትን አዘወትር ነበር ። በተለይ ብሔራዊ ቡድናችን ጨዋታ ሲኖረውና ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ግጥምያ ሲኖራቸው አልቀርም ነበር ።ታዲያ በስቴድየሙ ቆይታዬ የሚያረካኝ ከጫወታው ይልቅ ከመስመር ያልወጡ የደጋፊዎች ብሽሽቅ ፣ ቀልድና ትርርብ ነበር ። ከሁሉም ከሁሉም ደስ የማይልና ጋጠወጥ ድርጊት ሲያጋጥም ታዳምያኑ በሙሉ በአንድ ድምጽ የሚያሰሟት የተቃውሞ መዝሙር መቼም ቢሆን አልረሳትም ። ትዝም ትለኛለች ። "አቤት ቆሻሻ ፣ አቤት ቆሻሻ ፣ አቤት ቆሻሻ " አቤት . . .እንደ አጋጣሚ ሆኖ ወጉ ደርሶኝ ቃሊቲን በጎበኘሁ ጊዜም ይህችን "ቆሻሻ " የምትባለውን ቃል በተደጋጋሚ የሚጠሩበትን ሰዎች አይቻቸውም ነበር ። እነዚህም " ቆሻሻ " ተብለው የሚጠሩ ሰዎች በግረሰዶማዊነት ተይዘው የተፈረደባቸው ሰዎች ናቸው ።" ቆሻሾቹ " ማደሪያቸው ሽንት ቤት ፤ መዋያቸው የቆሻሻ ገንዳ ስር ነበር ። ይህን ሁኔታ መንግስት አዝዞ በወንጀላቸው እንዲቀጡ የወሰመባቸው ሳይሆን እስረኛው በራሱ ህግ አውጥቶ ድርጊቱን መፀየፉንና በኢትዮጵያም የተጠላና ሥፍራ የማይሰጠው መሆኑን ማሳየቱና ማረጋገጡም ነው ። 


እነዚህን በቃሊቲ " ቆሻሾች " ተብለው የሚጠሩትን መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ "ቀላጮች " እያለ ይጠራቸዋል ። " . . . አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ" 1ኛ ቆሮ 6፣9 ይሁንና ዓለም በተባለች በሰፊዋ ስታዲየም ዛሬ ዛሬ ደግሞ የሚገራርሙ ነውረኞችና ቆሻሻ ድርጊት ፈጻሚዎች ከሚገባው በላይ ቁጥራቸው እጅጉን ከፍ ብሎ በመታየት ላይ ነው ። በተለይ በሀገራችን በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ ይህ አስያፊ ድርጊት እጅግ በረቀቀ መንገድ እንዲስፋፋ እየተደረገ መሆኑን ማሳያ የሚሆኑ ዋቢዎችን መጥቀስ ይቸላል ። ድርጊቱን አስከፊ የሚያደርገው ደግሞ የድርጊቱ ፈጻሚዎች በተለየ ሁኔታ ለዚህ ቆሻሻ ተግባር የሚመለምሉት ጨቅላ ህጻናትን መሆኑ ነው ። በተለይ እንደ አባት የሚታይ መምህር ለትምህርት የላካችሁትን ጨቅላ ልጃችሁን ሲጫወትበት መስማት ይዘገንናል ። ባለፈው ሰሞን አንድ መምህር ይህን ቆሻሻ ተግባር በህጻናት ልጆች ላይ ፈጽሞ በመገኘቱ በፍርድቤት የነበረውን ክርክር ላየ ድርጊቱ ወደፊት ከባድ እየሆነ ለመምጣቱ ምልክትም ነው ። የአውራ አምባው ዳዊት ከበደ በፌስቡክ ገጹ ላይ በግልጽ ይህ አስፀያፊና ቆሻሻ ተግባር በውቢቷ ሀዋሳ ከተማ በግልጽ በተከፈተ የመዝናኛ ክለብ ውስጥ ለውጭ ሀገርና ለሀገር ውስጥ ቆሻሾች ህጻናትን እንደሚቀርቡና እንደሚቸበቸቡ የክለቡን ስም ጠቅሶ መዘገቡን ስናይ በጣም ያስፈራል ። ይህ ድርጊት ሲፈጸም የአካባቢው መስተዳድር አያወቀውም ለማለት አይደፈርም ።

Monday, March 07, 2016

ደጉ ሳምራዊ

እነሆም አንድ ሕግ አዋቂ ፈሪሳዊ ኢየሱስን ሊፈትነው ተነስቶ፦ መምህር ሆይ የዘለዓለምን መንግስት እንድወርስ ምን ላድርግ? አለው። እርሱም በሕግ የተጻፈው ምንድር ነው? እንዴትስ ታነባለህ?አለው። ፈሪሳዊውም መልሶ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ኀይልህም ውደድ፣ባለእንጀራህን እንደርስህ  ውደድአለው። ኢየሱስም እውነት መለስህ ይህንን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህአለው። ፈሪሳዊው ግን ራሱን ሊያጸድቅ ወዶ ነበርና ኢየሱስን ባለንጀራየስ ማን ነው ? አለው። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለ አንድ ሰው ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ወረደ በወንበዴዎችም እጅ ወደቀ፤እነርሱም ደግሞ ገፈፉት፤ደበደቡትም፤በህይዎትና በሞት መካከልም ትተውት ሄዱ። ድንገትም አንድ ካህን በዚያ መንገድ ወረደ፤አይቶትም ገለል ብሎ አለፈ። እንዲሁም አንድ ሌዋዊ ወደዚያ ስፍራ መጣና አይቶት ገለል ብሎ አለፈ። አንድ ሳምራዊ ግን ሲሄድ ወደ እርሱ መጣ አይቶትም አዘነለት፤ቀርቦትም ዘይትና የወይን ጠጅ በቁስሎቹ ላይ አፍስሶ አሰራቸው፤በራሱ አህያም ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች መቀበያ ወሰደው ጠበቀውም። በማግስቱም ሁለት ዲናር አውጥቶ ለባለቤቱ ሰጠና 'ጠብቀው ከዚህም በላይ የምትከስረውን ሁሉ እኔ ስመለስ እከፍልሃለሁ' አለው። እንግዲህ ከእነዚህ ከሦስቱ በወንበዴዎች እጅ ለወደቀው ባልንጀራ የሆነው ማንኛው ይመልሃል? አለው  እርሱም ምህረት ያደረገለትአለ። ኢየሱስም ሂድ አንተም እንዲሁ አድርግአልው።

በሕይዎት ጎዳና ስንጓዝ ምን እንድሚያጋጥመን አንውቅም። ቀደም ሲል በቀረበው ታሪክ ውስጥ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ይጓዝ የነበረው ሰው መጨረሻ አስከፊ እንደነበር አይተናል። ይህ ሰው ምን እንደሚያጋጥመው ቀደም ብሎ የተረዳ ቢሆን ኖሮ ጉዞውን በሌላ አቅጣጫ ወይም በሌላ ቀን ባደረገ ነበር። በህይወታችን ብዙ ፈተናወች ይገጥሙናል። ብዙ ጊዜ ወደፊት የሚገጥመን ነገር ምን እንደሆነ ሳናውቅ የጉዟችንን መስመር እንወስናለን። ሕይወት የእጣ ፈንታ ጉዳይ እንደመሆኗ አንዳንዴ መልካም ነገር አንዳንዴ ደግሞ ክፉ ነገር ያጋጥመናል። ምርጫችን ጥፋትን ሊያስከትልብን ይችላል፤ሞትን እስከማስከተል ድረስ። አንዲት የቤት እመቤት ከዕለታት  አንድ ቀን ያጋጠማቸውን ታሪክ እንደሚከተለው ይገልፃሉ። ባልፈው ሳምምንትአሉ አንድ ወጣት ልጅ የቤቴን በር አንኳኳ። በሬን ከፍቸ ስጠይቀው ስሙንና የዩኒቨርሲቲ ተማሪ መሆኑን የሚገልጽ መታወቂያ ወረቀት አውጥቶ አሳየኝ። ሥራ ፈላጊ መስሎኝ ለእርሱ የሚስማማ ሥራ እንደሌለኝ ገልጨለት መታወቂያውን ስመልስለት ሌላ ወረቀት በተጨማሪ አውጥቶ አሳየኝ። ሥራ አይደለም  የምፈልገው የእኔ እናት እባክዎን ሊረዱኝ ይችላሉአለኝ። የሰጠኝን ወረቀቅት ስመለከት የኤች አይ ቪ ቫይረስ በደሙ እንዳለብት አወቅሁ።


ቀደም ሲል አንዲት የሴት ጓደኛ ነበረችኝ እናምብሎ ሊቀጥል ሲል አቋረጥሁትና ይብቃህ የኔ ልጅ ሁሉንም ነገር ልትነግረኝ አያስፈልግምአልሁት። እባክዎ እናቴ ሰውነቴ በበሽታው እጅግ ተዳክሟል፤ሆኖም አገሬ መግባት አለብኝ ወደ አገሬ የምሄድበት ጥቂት ገንዘብ እንዲሰጡኝ እለምነዎታለሁአለኝ። ልጁን በጥሞና ተመለከትሁት፤ ዕድሜው ሃያወቹ ውስጥ ያለ ይመስላል፤ሰውነቱ ግን በበሽታው ተጎድቶ የደከመና የመነመነ ነው። ለጉዞው እንዲሆነው በማለት ጥቂት ገንዘብ ሰጠሁት፤እንዲሁም ምግብ አቀረብሁለት። እግዚአብሔር ይስጥዎ በጣም አመሰግናለሁ ውለታወን መቸም አልረሳውምብሎኝ ሄደ። ለዓይኔ እየራቀ ሲሄድ እንባየን መቆጣጠር አልቻልሁም። ወጣቶችን በአፍላ የምርታማነት ዘመናቸው የሚቀጭ እንዴት ያለ በሽታ ነው? የዚህ ልጅስ ህይወት ምን ትርጉም ይኖረዋል? ልጃቸውን ለትልቅ ደረጃ የተመኙት ወላጆቹስ በዚህ ሁኔታ ሲቀበሉት ምን ዓይነት ከባድ ኀዘን ይሰማቸው ይሆን?ብዬ አዘንኩ። ይህ ወጣት ግን አንድ ፍላጎት ብቻ ያለው ይመስላል አገሩ ገብቶ መሞት።


1) እርስዎ ከላይ  በታሪኩ በተጠቀሱት በቤት እመቤቲቱ ቦታ ቢሆኑ ምን ያደርጉ ነበር?  ወጣቱን  ዘወር በል  ብለው ያባርሩት ነበር ወይስ እንደ ወይዘሮዋ ምግብና ገንዘብ ይሰጡት ነበር?
2) በወላጆቹ፣ በእህትና በወንድሞቹ ቦታስ ቢሆኑ ወደ ቤት ተመልሶ ሲመጣ  እንዴት ነው የሚቀበሉት?
3) እንዲህ ዓይነት ሁኔታ አጋጥሞዎት ያውቃል?
4) እርስዎ እንደ ወጣቱ ላለመሆን ምን እያደረጉ ነው?
5) ኤች አይ ቪ እያደረሰ ስላለው ችግር ያለዎት አስተሳሰብ ምንድን ነው?

Tuesday, March 01, 2016

አድዋ - ያባከንነው ድላችን

ይህች ሀገር ብዙ የተከፈለባት ምድር ናት! ለውድቀቷ የተጉ የመኖራቸውን ያህል፣ ብዙዎች ሕይወታቸውን ከፍለው ለዛሬ ያበቋት ሀገር ናት፡፡… እኒህ ባለውለታዎቿ ሰው እንደመሆናቸው፣ የሰው ልጅ በዘመኑ የሚፈጽመውን ስህተት የፈጸሙ ቢሆን እንኳን፣ እናት ላሏት ኢትዮጵያ የከፈሉት ዋጋ ከዋጋ በላይ ነው፡፡ ይህንን መካድ፣ አለማክበርና ማባከን አለመታደል ነው፡፡ ራስንም ለውርደት አሳልፎ መስጠት! ስለዚች ሀገር ነጻነትና ክብር ብዙዎች በብዙ መልኩ ደክመዋል፡፡ መከፋታቸውን ችለውና ከራሳቸው ሀገራቸውን አስቀድመው ስለ እሷ ታትረዋል፡፡ በክፉ ቀንም አንገታቸውን ለሰይፍ፣ እግራቸውን ለጠጠር፣ ደረታቸውን ለአረር ሰጥተው ስለ ክብሯ ወድቀዋል፡፡ “የዛሬን አያድርገውና” ለኢትዮጵያውያን ስለ ሀገር ክብርና ስለ ሕዝቦች ነጻነት ሕይወትን መክፈል ታላቅነት ነበር፡፡ በዚህ አብዝታ የተመካችው ንግሥት ጣይቱ፤ አያውቀንም ላለችው የኢጣሊያ መንግሥት ወኪል አንቶኔሊ እንዲህ ነው ያለችው፡- “… የኢትዮጵያን ሰው ባታውቀው ነው፡፡ ለሀገሩ መሞት ማለት ለሀበሻ ጌጡ ነው፡፡ ሂድ ባሻህ ጊዜ ተመለስ ተሰናድተን እንጠብቅሃለን፡፡”ይህች ሀገር ዛሬ ላይ የደረሰችው ብዙ ዋጋ ተከፍሎባት ነው፡፡ ከክፍያም በላይ የሕይወት ዋጋ ተከፍሎባት፡፡ በዚህም አባቶቻችን እኛን አልፎ የአፍሪካውያንን አንገት ከተደፋበት ቀና ያደረገ፣ ዓለምንም “አጃዒብ” ያሰኘ አኩሪ ገድል ፈጽመዋል። ይህ ማንም የማያብለው የታሪክ ሀቅ ነው፡፡ ደረቅ ሀቅ!


ያም ሆኖ ታላላቅ ገድሎቻችንን ልናከብራቸውና ልንማርባቸው ሲገባ፣ ከንቱ እጅ እንደገባ ወርቅ ሁሉ አልባሌ ቦታ ተትተውና ቸል ተብለው ባክነዋል። ድሎቻችን ወደ ፊት መስፈንጠሪያችን ሊሆኑ ሲገባ ግብ የለሽ የቸከ ተረት አድርገናቸዋል። ድሎቹ የሰጡንን መነቃቃትና አቅም ከድርጊት ይልቅ በመተረት እናባክናለን፡፡ ለዘመናት እየሆነ ያለው ይኸው ነው፡፡ እውነቱን መቀበል ቢገደንም ቅሉ፣ እየሆነ ያለው እንዲሁ ነው፡፡ ድሎቻችንን ለዘመናት አባክነናል፡፡ አሁንም ለመማር ዝግጁ አንመስልም። በዓለም የነጻነት ታሪክ ውስጥ እንደ ተአምር ከሚቆጠሩት ክስተቶች አንዱ የሆነው አንጸባራቂው የአድዋ ድልም እንዲሁ ከዚህ መባከን አላመለጠም።… አድዋ! ስለ አድዋ ድል በየጊዜው የሚባለውን ሰብስበን እንበለው፡፡ የአድዋ ድል ነጮች የጥቁር ህዝቦች የበላይ ነን ብለው ለዓመታት ቀንበራቸውን ባጸኑበት፣ ጥቁሮችም ይህንኑ አምነው ለዘመናት በተገዙበት ዘመን ሀበሾች በነጮች ላይ የተቀዳጁት አንጸባራቂ የነጻነት ድል ነው፡፡… ይህ ክስተት የዓለምን አስተሳሰብ ቀይሮአል፡፡ እንኳንም በባርነት ቀንበር ተቀይደው የነበሩትን ጥቁሮች ቀርቶ የቅኝ አገዛዙ ተዋናዮቹን ሳይቀር እምነታቸውን አስፈትሾአል፡፡