Tuesday, December 31, 2019

???


ግዳይ አስቀምጦ ለሕይወት መታጨት
ዘር ቀለም ሳይመርጡ ሰው ከእንስሳ መቅጨት
ፀሐይ ቁር ሳይፈሩ ግዑዝ ሆኖ ማርጀት
ጠፋች ሞተች ሲባል
ሰላም ለከ ብሎ ዳግመኛ መደርጀት
አጥፍቶ አለመጥፋት ልምድሽ ሆኖ ኑሮ
ኑሮ ኑሮ ኑሮ
ካንቺም በላይ ጀግና ሲመጣ ሲፕሮ
ቁርባ ቁርቢት ቁርጥሽ ነው ዘንድሮ

ቱ!

ያልታደለች ጉብል እድል የጠመማት
በአመንዝራ ዲያቆን
ተደፈርኩኝ ብላ ነገሩ ሲገርማት
የነፍሷ ጠባቂ ካህኑም ደገማት
በየት በኩል አልፎ ፈጣሪዋስ ይስማት?
ቱ!

Sunday, December 15, 2019

ጭንቃጭንቅ ዜና


በማድጋ ዞን ሽንክላ ወረዳ ጭንቁላ ቀበሌ የሽንትቤት ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ።

አ.ዲ.መ.መ ዘለፋ 8/900010 ዝንጠላ፡ ዲስኩር። በማድጋ ዞን ሽንክላ ወረዳ ጭንቁላ ቀበሌ የሽንትቤት ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ መዋሉ ተገለጸ። የቀብሌው ሊቀመንበር አቶ እንዳመጣው ደባልቄ በበዓሉ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደተናገሩት የዘንድሮውን በዓል ከባለፉት ለየት የሚያደርገው ከምንትስ ሚሊዬን በላይ ሶፍትና ወደ ብጥስጥስ የሚጠጉ የሽንት ቤት ወረቀቶችን ለማከፋፈል የቻልንበት መሆኑ ነው ብለዋል ። በበዓሉ ለረዥም ስዓት ሽንት ቤት ውስጥ በመቀመጥ የተሻለ ልምድ ላካበቱ ሞዴል ሽንታምና ተቅማጣም ወጣቶች የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ሌሎቻችንም የእነዚህን ግንባር ቀደም ወጣቶች አርዓያ ልንከተል እንደሚገባ ተጠቁሟል። ከተሸላሚ ቤተሰቦች አንዷ የሆኑት ወይዘሮ ትንጓለል አዝብጤ በበዓሉ ላይ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው በቅርቡ የሚከበረውን የወስፋትና ወስፋታሞች ቀን ለማክበር ዝግጅት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ከዜናዎቹ ጋር እሣቱ ለብልቤ ነበርሁ ሰላም

ኑሮ ተወደደች ደስታ ተሰደደች
እኔ እበላው ሳጣ ሚስቴ ልጅ ወለደች
ስኳር ጣሪያ ነካ
ግፊቴም ከፍ አለ ብላችሁ ምትፈሩ
ተካፍሎ ማደር ነው የጤና ምስጢሩ
መልካም ዕለተ ሰንበት

Tuesday, December 10, 2019

"መልካም ያደረጉልንን ሳናመሰግናቸው ይች ቀን አትለፍ" .



የዝቋላ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአ/ብ/ክ/መ ጤና ቢሮ ስር ከሚገኙ ሆስፒታሎች አንዱ ሲሆን ለማህበረሰቡ እየሰጠ ያለውን ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማሻሻልና አገልግሎቱ በንባብ የዳበረ ብሎም በምክንያትና በእውቀት የተመሰረተ ይሆን ዘንድ EHSTG Reform በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት በሆስፒታሉ ውስጥ ቤተ-መጽሐፍት እንዲኖረን ለማድረግ ፕሮጀክት ቀርፀን እየሰራን መሆኑ ይታወቃል።


በዚህ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችሉ የህትመት ውጤቶችን ለማሰባብሰብ ተችሏል። ስማቸው ከታች ለተዘረዘሩትና ለዚህ ዓላማ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ላደረጉ አካላት ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን አሁንም ቢሆን ሥራው ተጀመረ እንጅ አላለቀምና “እውቀት እንረዳለን” የምትሉ ሁሉ በስልክ ቁጥር +251918666678 ወይም በኢሜይል getanehkassie@gmail.com ልታገኙን እንደምትችሉ ለመግለፅ እንወዳለን።



ምስጋና
1.ለወ/ሪት ሳምራዊት እስጢፋኖስ
2.ለደራሲ ይስማዕከ ወርቁ
3.ለዶ/ር ትዕግስት ስለሺ
4.ለአቶ ዘላለም ጥላሁን
5.ለወ/ሮ ዓለሚቱ ደሴ
6.ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጤና ሚኒስቴር
7.ለሆስፒታላችን ሰራተኞች በሙሉ
.
ዶ/ር ጌታነህ ካሴ
የፕሮጀክቱ አስተባባሪ






የድጋፍ ጥያቄ