Tuesday, December 10, 2019

"መልካም ያደረጉልንን ሳናመሰግናቸው ይች ቀን አትለፍ" .



የዝቋላ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአ/ብ/ክ/መ ጤና ቢሮ ስር ከሚገኙ ሆስፒታሎች አንዱ ሲሆን ለማህበረሰቡ እየሰጠ ያለውን ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማሻሻልና አገልግሎቱ በንባብ የዳበረ ብሎም በምክንያትና በእውቀት የተመሰረተ ይሆን ዘንድ EHSTG Reform በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት በሆስፒታሉ ውስጥ ቤተ-መጽሐፍት እንዲኖረን ለማድረግ ፕሮጀክት ቀርፀን እየሰራን መሆኑ ይታወቃል።


በዚህ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችሉ የህትመት ውጤቶችን ለማሰባብሰብ ተችሏል። ስማቸው ከታች ለተዘረዘሩትና ለዚህ ዓላማ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ላደረጉ አካላት ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን አሁንም ቢሆን ሥራው ተጀመረ እንጅ አላለቀምና “እውቀት እንረዳለን” የምትሉ ሁሉ በስልክ ቁጥር +251918666678 ወይም በኢሜይል getanehkassie@gmail.com ልታገኙን እንደምትችሉ ለመግለፅ እንወዳለን።



ምስጋና
1.ለወ/ሪት ሳምራዊት እስጢፋኖስ
2.ለደራሲ ይስማዕከ ወርቁ
3.ለዶ/ር ትዕግስት ስለሺ
4.ለአቶ ዘላለም ጥላሁን
5.ለወ/ሮ ዓለሚቱ ደሴ
6.ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጤና ሚኒስቴር
7.ለሆስፒታላችን ሰራተኞች በሙሉ
.
ዶ/ር ጌታነህ ካሴ
የፕሮጀክቱ አስተባባሪ






No comments:

Post a Comment