Sunday, December 15, 2019

ጭንቃጭንቅ ዜና


በማድጋ ዞን ሽንክላ ወረዳ ጭንቁላ ቀበሌ የሽንትቤት ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ።

አ.ዲ.መ.መ ዘለፋ 8/900010 ዝንጠላ፡ ዲስኩር። በማድጋ ዞን ሽንክላ ወረዳ ጭንቁላ ቀበሌ የሽንትቤት ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ መዋሉ ተገለጸ። የቀብሌው ሊቀመንበር አቶ እንዳመጣው ደባልቄ በበዓሉ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደተናገሩት የዘንድሮውን በዓል ከባለፉት ለየት የሚያደርገው ከምንትስ ሚሊዬን በላይ ሶፍትና ወደ ብጥስጥስ የሚጠጉ የሽንት ቤት ወረቀቶችን ለማከፋፈል የቻልንበት መሆኑ ነው ብለዋል ። በበዓሉ ለረዥም ስዓት ሽንት ቤት ውስጥ በመቀመጥ የተሻለ ልምድ ላካበቱ ሞዴል ሽንታምና ተቅማጣም ወጣቶች የማበረታቻ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን ሌሎቻችንም የእነዚህን ግንባር ቀደም ወጣቶች አርዓያ ልንከተል እንደሚገባ ተጠቁሟል። ከተሸላሚ ቤተሰቦች አንዷ የሆኑት ወይዘሮ ትንጓለል አዝብጤ በበዓሉ ላይ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው በቅርቡ የሚከበረውን የወስፋትና ወስፋታሞች ቀን ለማክበር ዝግጅት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ከዜናዎቹ ጋር እሣቱ ለብልቤ ነበርሁ ሰላም

No comments:

Post a Comment