Tuesday, May 08, 2018

ተፈስሒ በሏት

ፀሐይን  የምትወልድ ውብ ደማቅ ጨረቃ፣
ቀድመው ያኸለሟት ቴክታና ጴጥርቃ፤
እናትና ገረድ ድንግልና ሰማይ፣
ሐመልማልና እሣት ሐርና ወርቅ ፈታይ፤
መሰረታቲሃ ውስተ አድባር  ውእቱ፣
ብሎ ያወደሳት ዳዊት በትንቢቱ፣
ተወልዳለችና የአምላክ እናቱ፣
ከበሮ ይመታ ይድመቅ ማኅሌቱ።
ጠላት ኃይሉን ይጣ ይንቀጥቀጥ ዓለሙ፣
የሕርያቆስ  ልጆች ድምፃችሁን አሰሙ፣
ተፈስሒ በሏት ካህናት አዚሙ።
ትንቢት  ተፈፅሟል ያስተጋባ ቃሉ፣
ተወልደ ብዕሲ በውስቴታ በሉ።
ጌች ቀጭኑ ዘታችቤት ግንቦት 1/2010 ዓ.

No comments:

Post a Comment