Thursday, July 18, 2019

....አንተ ማለት....

በኦነግ ሸማ እቃ  ኩታህ ተሸምኖ
በህውሓት አርማ ገላህ ተጀቡኖ
አንተ ማለት አብን አንተ ማለት ማለት ፋኖ
መላሾ እያሳዬ ያሻው የሚነዳህ
ግጦሽ ስትከተል ህሊናህ የከዳህ
የግሌ ምትለው እውነት የለህ አቋም
ትላንት በጌታ ስም ዛሬ ደግሞ አቋቋም
ጥዋት ቤተመቀድስ ከሰዓት ቃልቻ
አርሴማን  ከዙቤር አስረህ በጋብቻ
እምነት ምናባቱ ገንዘብ ያስገኝ ብቻ
ዶግማ ገደል ይግባ  ይቀንቅን ቀኖና
አንተ ማለት ሳንቲም አንተ ማለት ዝና
በአብ ስም ጀምረህ በአላህ የምትጨርስ ሲራራ ነጋዴ
እንደ ልመና እህል የተደባለቀው ምርትህ ተቸርችሮ አላለቀም እንዴ?

 ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማን ነው?  አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል። ድቃቂ ሳንቲምና ዝናን ፍለጋ እዛም ቤት እዚህም ቤት ለምትልከሰከሱ ባተሌዎች! መልካም እለተ ሰንበት

07/11/2011 ዓ.ም
ዝቋላ ሆስፒታል 

No comments:

Post a Comment