Wednesday, April 17, 2019

ይቅር ብዬሃለሁ

የእናት ሀገሩን ሀብት ስዊዝ አስቀምጦ
በፈጣሪ ቁጣ ሲወርድ ቂሊንጦ
ጠበቃ ከመንግሥት ቅጥር እንደተመኘው
እንደ ሜቴክ አዛዥ እንደ ክንፈ ዳኘው
የልፋቴን ዋጋ ቅርጥፍ አርገህ በልተህ
መመረቂያ ፎቶ መፅሔቴን አግተህ
ይቅርታ ጠይቀኝ ብለህ የላክህብኝ
የሰውነት እንጅ
የአስተሳስብ ቅጥነት ከቶ እንደሌለብኝ
የቅርብ ጓደኛ ነጋሪ ጠፍቶ ነው
ወይስ ፍቅረ ንዋይ መስሚያህን ደፈነው
ይልቁንስ ስማኝ ልንገርህ ወዳጄ
በተዓምር ስትገባ መጎረጫህ ከእጄ
ድንጋይ ተሸክመህ ባትቆምም ከደጄ
ወቅቱ የመደመር ነው ሲሉ ሰምቼ
ይቅር ብዬሃለሁ ሁሉን ነገር ትቼ
ታኅሣስ 8/2011 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment