Saturday, March 25, 2017

ወርቃማ አባባሎች

👉 የምንፈፅመው ጥሩም ሆነ መጥፎ ነገር የህልውናችን ነፀብራቅ ነው፤ስለሆነም እኛነታችንን ደብቀን መሰቃየት የለብንም፤መጥፎ የምንለውን አምቀን ጥሩ የምንለውን ብቻ የምንተነፍስ ከሆነ ውስጣችን ገምቶ ደማችን ይደፈርሳል።
👉 ለውጥ ማለት በጠባይም ሆነ በአሰራር ራስን መቀየር ፣አዲስ ሁኔታ ማምጣት ማለት ነው።ለውጥ በጽኑ ውሳኔ  ላይ የሚመሰረት  ራስን ለመቀየር  የመፈለግና የመነሳሳት ጠንካራ አቋምና ድርጊት ነው።ለውጥ ምኞትና ተስፋን የሚያዘወትሩ የማያዩት በራሳቸው መቆም የማይችሉና ድጋፍ ፈላጊ ደካሞች ደግሞ ምን ጊዜም የማይደርሱበት የውጤት መንገድ ነው።
👉 ከሰዎች ጋር በመኖር  የሰዎችን ችግር ለመፍታት መሞከርና መርዳት የተሻለ ጽድቅና  መንፈሳዊነት ነው። 
👉 ስህተትና በደል ከሰው ልጅ ጋር የሚኖሩ ደካማ ባህርያቱ ናቸው ። ስህተትን አውቆ መጸጸትና ከስህተቱ ለመማር መዘጋጀት ግን እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፤በሕሊና ወቀሳ የቆሰለ ልቦናንም ያድናል ። 
👉 የአወዳደቁ አይነት በመለያየቱ እንጅ በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ ውድቀት አለ፤ትልቁ ተግባር ግን ከወደቁበት መነሳትና  ራስን ማስተካከል ነው።
👉 ብቸኝነትህን የሚያመጣው ብቻህን መሆንህ አይደለም፡፡ አብሮህ ያለውን አለማወቅህ እንጂ፡፡ አካባቢህን ካላወቅህ በሰዎች መካከል ሆነህ እንኳን ብቻህን ትሆናለህ፡፡ አካባቢህን ካወቅከው ግን መቼም ብቻህን አትሆንም፡፡
👉 ራሷን ዝቅ ያደረገች ማሽላ  አንድም ከወፍ አንድም ከወንጭፍ ታመልጣለች።
👉 ለአንድ ሰው የስራውን ግብ ከፍ ፡ጊዜውን ደግሞ አጠር አድርገህ ከሰጠኸው የፈለግኸውን አከናውኖ ይቆይሃል።
👉 የሕጻንነት ወዳጇን የምትተው የአምላኳንም ቃልኪዳን የምትረሳ ሴት ቤቷ ወደ ሞት አካሄዷም ወደ ሙታን ጥላ ያዘነበለ ነው።ወደ እርሷ የሚገቡ ሁሉ አይመለሱም፥የህይዎትንም ጎዳና አያገኙም።
👉 ፍቅር በተዘጋ ቤት ውስጥ እንደሚያነዱት ሻማ ነው።በርና መስኮት ሲከፈት ሻማው ለንፋስ እንደሚጋለጥ ሁሉ ዓይንና ጆሮ ሲከፈት ደግሞ ፍቅር ለወሬኞች ይጋለጣል። 
👉 የፖለቲካ ጭቆና በበዛበት ሀገር ውስጥ፣ወሲባዊ ልቅነት የመጨረሻው የነጻነት አማራጭ ተደርጎ ይወሰዳል።አመንዝራነት ዜጎች ሌላው ቢቀር  ብልታቸው በመንግሥት ቁጥጥር ሥር አለመሆኑን የሚያሳዩበት መንገድ ነው።

No comments:

Post a Comment