Monday, July 09, 2018

ቅኔ ነሽ

የጠገበው ሲሄድ የራበው ሲመጣ
ሲስተር አ'ዘነጋሽ ምጣድሽ አይውጣ
የሚል ግጥም ልፅፍ ልቀኝ ያመረኝና
ቃላት አቅም አጥተው ይሆናሉ መና
የማምዬን ናፍቆት ፍቅርሽ የሚያስረሳ
ለቁርስ የጋገርሽው የሚተርፍ ለምሳ
በፈተና ብዛት ትጥቅሽ ያልተፈታ
የጠላትን ጉራ ትዕግስትሽ የረታ
የሥጋ ፍላጎት ደፍሮ ያልፈተነሽ
ረሃብ ውኃ ጥም ያላመነመነሽ
ወርቅሽ ያልተፈታ አንች እኮ ቅኔ ነሽ
ታችቤት : ሰኔ 30 /2010 ዓ.ም
 እንኳን ደስ ያለሽ ለማለት ያህል

No comments:

Post a Comment