Wednesday, July 11, 2018

የጋብቻ ጥያቄ

ቀን 3/11/2010 ዓ.ም
ለፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ
አስመራ


                 ጉዳዩ፦ የጋብቻ ጥያቄን ይመለከታል
እንደሚታወቀው እኛ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን በኢኮኖሚ፣ በባህል፣ በጋብቻ የተሳሰረ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለን
ህዝቦች ነን። ከዓመታት በፊት በሁለቱ ህዝቦች መካከል የተፈጠረው ግጭት ወይም አለመግባባት የብዙ ወጣቶችን ህይወት
የቀጠፈና ደም ያፋሰሰ እንዲሁም ሁለቱን ህዝቦች ፊት ያዟዟረ ቢሆንም፤ በቅርቡ የተጀመረው ጥላቻን በምህረትና በይቅርታ
የመሻር ሂደት ሁላችንንም የደስታ እንባ አስነብቶናል። እኔም ዶ/ር ጌታነህ ካሴ የተባልሁት ግለሰብ በጅማ ዩኒቨርሲቲ
የህክምና ማዕከል የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪ ስሆን በክቡር ዶ/ር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዓብይ አህመድ የተጀመረውንና
በሃገር አቀፍ ደረጃ ጎልቶ በመታየት ላይ ያለውን የሰላም፣የፍቅርና የመደመር መርህ እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት
የበለጠ ለማጠንከር ሁለቱን ህዝቦች ልብለልብ ለማስተሳሰር ክቡርነትዎ የጋብቻ ጥያቄዬን ተቀብለው አንዲት ውብ ሰሜናዊት
ኮከብ ጽብቅቲ ዓይናማ ሹርቤ ቆንጆ ልጃገረድ ይሰጡኝ ዘንድ በትህትና እጠቃለሁ።
ከሰላምታ ጋር
              ዶ/ር ጌታነህ ካሴ(MI)
       ጅማ ኢትዮጵያ

ግልባጭ
ለኤርትራውያን ልጃገረዶች በሙሉ

No comments:

Post a Comment