Thursday, July 13, 2017

ማን ዘርቶ ማን ያጭዳል?

አንድ አርሶ አደር  ያልዘራውን ስንዴ ወይም አርሞ ኮትኩቶ ያላሳደገውን አዝመራ መከር ሲደርስ እሰበስባለሁ ብሎ ሊከራከር እንደማይችል ማንም ሰው የሚያውቀው ጉዳይ ይመስለኛል። ታዲያ  በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ተቸጋግሮ  ሲማር፣ እንደ አጋጣሚ በንባብ ተጠምዶ ሳያስበው የካፌ ሰዓት በማለፉ ጾሙን ድፍት ብሎ ሲያድር፣ እንደ ሌሎች ሻይ ቡና ብሎ ወደ ንባብ የሚመለስበትን ቀን ሲናፍቅ፣ ይቺ የሻይ ቡና ይቺ ደግሞ የሳሙና  ትሁንህ ያላሉትን ተማሪ ዛሬ ላይ ዳቦ ጋግሬ፣ ጠላ ጠምቄ፣ ሙክት አርጄ፣ ፍሪዳ ጥዬ አስመርቅሀለሁ ማለት የሞላኝ የደላኝ ሀብታም ነኝ ብሎ ለመመፃደቅ ካልሆነ በቀር ሌላ  ምን ትርጉም ይኖረዋል? ተቀያሪ በሌላቸው ልብሶቹ የጓደኞቹ መሳለቂያ  እስከሚሆን ሲቸገር  ለደብተር እና ለእስክርቢቶ እጁን ያልዘረጋ ዘመድ የምረቃ ዕለት እንደ ድንገት የ90 ብር አበባ እና የ5ሺህ ብር ስማርትፎን ይዞ ማዘጥዘጡስ ምን ሊበጅ? ማን የዘራውን፣ ማን አርሞና ኮትኩቶ  ያሳደገውን፣ ማን ያጭዳልያልዘሩትን አጫጅ ከመሆን ይሰውረንማ አቮ !!! ለማንኛውም ተመራቂዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ብያለሁ።
 ሰኔ 1/2009 .ም :ሲስኮ

No comments:

Post a Comment