Wednesday, July 05, 2017

🎓አውቆ የደደበ🎓

ለሰው ግድ የሌለው አምላኩን ማይፈራ፣
እንኳን ለወንድሙ ለእናቱ ማይራራ፣
ግን ደግሞ !
“የተማረ” ተብሎ በማዕረግ ሚጠራ፤
ጭንቅላቱ ከስቶ ምላሱ ያበጠ፣
በሰይፍ አንደበቱ እልፍ የቆረጠ፣
አብዶ ያልወጣለት ምራቁን ያልዋጠ፣
የትህትናን ደጅ እግሩ ያልረገጠ፤
ከፍቅር ገበታ  እጁ ያልዘገነ፣
የተስፋው ጭላንጭል ከፀጉር የቀጠነ፤
በምስኪኖቹ ላብ ከርሱን የሚሞላ፣
ሰቆቃ እና ስቃይ የሚመስለው ተድላ፤
በወይን ጠጅ ያይደል በግፍ የሰከረ፣
በክፋት ተሞልቶ ጢምብራው የዞረ፣
አውቆ የደደበ  ስንት ማይም አለ!
©ጌች ቀጭኑ ሰኔ 27/2009 ዓ.

No comments:

Post a Comment