Tuesday, June 02, 2015

ሰሳ


Yaya-Sanogo
በአንድ የክረምት ወራት ዝናብ እንዳባራ፣
ወጣ አልኩኝ ከቤቴ ቀለል ላለ ስራ።
በጠራው ሜዳ ላይ አንድ የሜዳ ሰሳ፣
አየሁ ሰርዶ ልትግጥ ስትወድቅ ስትነሳ።
አወ ራራሁላት ችግሯን አይቼ፣
ፈለግሁ ልመግባት ከስርዶው ነጭቼ።
ከአጠገቧ ሰርዶ ነቃቅየ ይዤ፣
እሥሥ ብይ ብየ ጋበዝኋትኝ በእጄ።
ጥላኝ ስላልሮጠች አልቆረጥሁም ተስፋ፣
እሷም ቀጥ እኔም ቆምሁ ፍጥጫው ተስፋፋ፣
ከመካከላችን እግር ነቃይ ጠፋ።
ካሰብሁኝ በኋላ አውጥቸ እና አውርጄ፣
ወሰንሁኝ ልሰጣት እኔው ግፋኝ ሂጄ።
አንድ እግሬን አንስቼ ወደ ፊቴ ስጥል፣
እሷም የኋላ እግሯን የኋሊት ስትነቅል።
የግራውን እግሬን ሳነሳው ለአንድ አፍታ፣
እሷም ሸርተት ስትል የኔን እግር አጥታ።
ስትሄድ ወደ ኋላ እኔም ስከተላት፣
በጨበጥሁት ሰርዶ ስጥር ላባብላት፣
ወደፊት አምጥቸ ከሳሩ ላበላት።
እሥሥ አንች ሰሳ ሰላም ነኝ አትፍሪ፣
አገሩም ሰላም ነው ሰውንም ድፈሪ፣
አንችም እንደ ሰወች በነጻነት ኑሪ።
ብየ ብቀባጥር አላዳመጠችም፣
አወ አትናገርም አልተናገረችም፣
ከኋላ ጉዞዋም ፈጽማ አልቆመችም።
እኔም ተስፋ ሳልቆርጥ እርሷም ስትጎትተኝ፣
ሚዳቆች ቡኸሮች ጮቤ እረገጡ፣
ከኋላዋ ካለው ከዱሩ እየወጡ፣
ለጎሪጥ እያዩዋት አልፈዋት እሮጡ።
አፌ ስራ አልፈታምጮሆ ይናገራል፣
ወደፊ ተራመጅ እንደነሱ ይላል።
እየጎተተችኝ በሃሳብ ተውጣ፣
ከስርዶው ልትጎርስ ወደፊት ስትመጣ።
ድንገት ሳታስበው ከጥንት ዘመን ጉድባ፣
ሁለት የኋላ እግሯ ሰርጎድ ብሎ ገባ።
በሁለቱ እግሮቿም ጋማቱን ጨብጣ፣
ሰማሁኝ ለእርዳታ ቃል ከአፏ ሲወጣ።
ጎትቸ ለማውጣት በተቻለኝ አቅሜ፣
ሁለት የፊት እግሯን ያዝሁ ተሽቀዳድሜ።
እየጎተትሁ ሽቅብ አንገቷ ሲወጣ፣
የዝንጀሮ መንጋ ከዋሻው ስር መጣ።
አንዱ አንዱን ረግጦ አንዱ በአንዱ ወጦ፣
አንደኛ ጅራቷን አንዱ እግሯን ጨብጦ።
ያን የገደል ዋሻ ተቆላልፈው ወጥተው፣
ፈለጉ ሊወስዷት ከመዳፌ አውጥተው።
ምን ሊያደርጋት ይሆን የዝንጀሮ መንጋ፣
ከመቸስ ወዲህ ነው የለመደው ስጋ።
ብየ እየጎተትኋት ወደታች ባፈጥ፣
የተራበ አንበሳ አየሁኝ ከዉስጥ።
እኔም ላላስበላት ስጎትት ስትወጣ፣
ጨለማው ተገፎ ታየኝ ቀን ሲመጣ፣
እኔ ብቻ ነቃሁ ሕልሜ ትርጉም አጣ።

No comments:

Post a Comment