Tuesday, June 02, 2015

የሌሊት ዜማዎች

ተዋናይ ነው አሉ፣
ሞትን የገዘተ ሰባት አመት ሙሉ።
ታዲያ ምን ይደንቃል፣
እንቅልፍን ገዘትሁት እኔ በምስኪን ቃል።
የእድሜወቼን እሸት ቢበላ ቢበላ፣
አሲዳም እንቅልፌ መቼም ከርሱ አይሞላ፣
መደቤን አፍርሼ ከህልሜ ልጣላ።
ተዋናይ ስለምን አምላክን ይከሳል፣
ሞት አንዴ ይመጣል ህልም ይመላለሳል።
መቃብርን ደፍኖ ሞትን በቁም አስሮ፣
ሰው ነፍሱን ይቀብራል ሕልሞቹን ቆፍሮ።
ተዋናይ ምርኮህን ልቀቀው ይፈታ፣
ና! እንቅልፍን እሰር በሞት እግሮች ፈንታ።
በአልጋ እቅፍ ለኖረ ጉድጓድ መች ይከብዳል፣
ከመቃብር ይልቅ ሕልም ይጎደጉዳል።

No comments:

Post a Comment