Tuesday, June 02, 2015

መሽቷል አትበል

በውድቅቱ አትከፋ
በጎህ መቅደድ አትጽናና፣
ብርሃን ለመመፅወት አትበል ቀና፣
የእኛ ፀሐይ ሐሩር እንጅ ብርሃን አትወልድምና።
መሽቷል አትበል ጀንበር ስትጠልቅ
ከዛጎሏ ውስጥ ገብታ፣
መሽቷል አትበል ፀሐይ ስትሞት
በከዋከብት ተተክታ፣
በውስጥህ ላለው ብርሃን
ግርዶሽ የሆንህ ለታ፣
ያን ጊዜ ሆኗል ጽልመት
ያን ጊዜ ሆኗል ማታ።
          ስብስብ ግጥሞች ፦በውቀቱ ስዩም
           

No comments:

Post a Comment