Monday, September 26, 2016

የነጋበት ማምሸት

እውነትን ተናግሮ የመሸበት ማደር፣
መባሉን ሰምተናል ትውፊቱ ሲነገር።
ዛሬ ጊዜው ከፍቶ ስንታይ የጎሪጥ፣
እውነቱን ተናግሮ አይረባም መጋፈጥ።
የመሸበት ማደር  ቀርቷል ትላንትና፣
እውነት ተናጋሪን ማን ያስመሸውና።
እንዲህ ሁኗል ዛሬ ተረቱ ሲለወጥ፣
እውነት የሚናገር እንዳወራ ያምልጥ።

ምንጭ ሀሞት የግጥም ስብስብ 
በኄኖክ ስጦታው

No comments:

Post a Comment