Tuesday, April 01, 2025

አትሂድ

 አትሂድ አትሂድ ብዬ ጮሄ ነበር ብሬን አንስቼ

የሀገርን ጥቅም የወገንን ፍቅር ባክብሮት አይቼ

አትሂድ ብዬ ነበር ወገቤን ታጥቄ

ሀገር ያለ እኛ ላብ እንዳትኖር አውቄ


ተው ብዬህ ነበረ 

ከልክየህ ነበረ

ከባህር የወጣ ተረቴን ተርቼ

ከመሄድ ሀሳብህ ላቅብህ ተግቼ


መንገዱ እሾህ በዝቶት ምን ጫማ ባይኖረን

ትቼ ልሂድ አትበል እንጥረገው አብረን

እያልኩኝ ወትውቼ

አሳስቼህ ነበር እኔም ተሳስቼ


እርግጥ

እርግጥ አትሂድ ብዬ ያኔ የፃፍኩበት

እርግጥ አትሂድ ብዬ ያኔ የፃፍኩበት

ብዕር የለም እንጅ ውብ ቀለም አልቆበት

ይታዘበኝ ነበር ይሄን መልሼበት 


ልክ ነበርክ አንተ

ኽም

እዚህ ለፍተህ ስትኖር ባገርህ አፈር ላይ

'አባን ከና' የሚል ያንተን ልፋት የሚያይ

አንዳችም ሰው የለም ህዝቡ ውጭ አምልኳል

ልቡ ተንበርክኳል

ላገር ስታነባ በጥቅም ይለካል

በነጻ ያላበህ በዶራል ይተካል

አሁን በቀደም ለት

ለቤታችን ምርጊት ያቦካናት ጭቃ

ብሎኬት ለማቆም ቦታው ተፈልጎ ተጣለች ተዝቃ

ተመስገን ማለት ነው ቀርቶ መማረሩ

ስንዝር መቀበሪያም ካልጠፋ ባገሩ

ተመስገን ነው ጥሩ

ለኑሮማ ሚሆን መሬት ማን አሲዞን

ቤታችን ወደ ላይ ቢቀርበን እግዜሩ

ወደላይ ነው ጥሩ

ወደ ላይ ወደ ላይ ወደላይ አሻቅቦ

አንደኛው ባንዱላይ ኑሮውን ደርቦ

......ህ........ም..........

እግዚያር ቀረበ ጸሎትህ ተሰማ

ባለ - ቤት ልትሆን ነው እዚሁ ከተማ

እሰይ፥ እሰይ እሰይ የምስራች ለነዋሪው ሁሉ

ሀገር ለወደደ ከነምናምኑ

ለደሃው የሆነ ደርሶ ለተገፋ

ፎቅ ቤት በያይነቱ መጣ በወረፋ

ሲባል ጆሮህ ሰምቶ

ከጸሎትህ ጋራ እጣ ፈንታህ ገብቶ

የጣ ቁጥር ይዘህ አመታት ቆይቶ

ቆይቶ ቆይቶ ቆይቶ ቆይቶ....ቆ...ይ...ቶ!

ቅድሚያ ይሰጥሃል ስትከፍል መቶ

እንኳን መቶ ቀርቶ የለህም ሰላሳ

በቃ እድልህን ጠብቅ

የሚያለማ መጥቶ ሰፈሩ እስኪነሳ

......እናልህ ወዳጄ........

ከዚህ ሁሉ ፍዳ ከዚህ ሁሉ ጣጣ

ምን አለበት አሁን ደርሰህ ብትመጣ

ምን ያደርግልሃል? ምን ያደርግልሃል? መሆን ያገር ዜጋ

ሞልቷል ትርፍ መሬት ክፍቱን የሚያዛጋ

ነጻ ሚሰጥህ ግን በሰው ሃገር ለፍተህ ላገኘኸው ጸጋ

እንዲሆንህ ዋጋ

......ህ........ም..........

ጠብታ ውሃ ነው ድንጋይ የሚበሳ

እንጩህ ዝምብለን ህዝብ እስከሚነቃ ሀገር እስኪነሳ

ብዬህ ነበር ያኔ አለማወቅ ደጉ

ለካስ ወርቁን ትቶ ለመዳብ ነው ጉጉ

ሀገር መሀል ሆነህ ሀገር መሀል ሆነህ

ለሀገር ስትጮህ፥የለም የሚያዳምጥ

ማዶ ስትሆን ነው የሹክሹክታህ ጉልበት ሀገር የሚለውጥ

ብትስቅ ብታለቅስ ሰዉ በወረፋ ሊያይህ የሚጋፋ

ዘፈንህ የሚያምር እስክሳህ የሚደምቅ

ካገር ስትወጣ ነው ጥበብህ የሚረቅ 

እድሜህን ቀርጥፈህ ብቶን ባለ ድግሪ

ማስትሬት ዶክትሬት ብትደክም ብትለፋ

እውነቱን ልንገርህ በሃገሬ ሂሳብ

ከውጪ የመጣ የሶስት ወር ኮርስ ነው ሚዛኑን ሚደፋ

.....ይሄወልህ ወዳጄ.......

ያገሬ ጎበዛት ህዝብ የምንላቸው

ያለኛ ጨውነት ጥፍጥናም የላቸው

ብለን ያንልላቸው

ባንተ ካገር መኖር ጉዳይም የላቸው

ምን ታሪክ ቢሰራ ነብይ በሀገሩ መቼ ይከበራል

ተረት እያወሩ

ጸበል ጓሮ አግኝተው ቁርበት ነከሩበት

በል እኔን አትስማኝ አንተ እወቅበት

......አሁን ሌላውን ተው........

ቀበሌ ሄደሃል ገጥሞህ አንዳች ጉዳይ

በሀገር ነዋሪ መሆንህ እንዲታይ

ይታወቅልህ ዘንድ የነዋሪ መግለጫ

ስጡኝ ብትላቸው

ሰው የለውም ቢሮው ባዶ መቀመጫ

አ ሁን ለሻይ ወጡ ጠጥተው እስኪመጡ

አንድ ሁለት ሶስት ሰአት አርፈው ይቀመጡ

ነገ ደግሞ የሉም ስለሚደክማቸው

እረፍት ላይ ናቸው

የሆነ ቀን ታመው ሌላ ቀን ረስተው

ወጡ ሳይፈርሙ ስብሰባ ላይ ናቸው

ስራ እያስቀደሙ

ስራ እያስቀደሙ፥ ምንድን ነው ስራቸው?

ዛሬም ከስብሰባ ነገም ካለቃ ጋር የሚያጣጥዳቸው

ያን ጊዜ ለምርጫ ቅስቀሳ ሲዞሩ

ያንተን መታወቂያ ባግባቡ ሊሰሩ

ነበረ ዲስኩሩ፣እሳቸው ግን የሉም

ባዶ ነው ወንበሩ

.......ህ........ም.........

ተዋቸው ተዋቸው ልንገርህ

ብሄድ ነው የሚያዋጣ

አለህ የሚልህ ከሌለ ምናል ካገር ብትወጣ

አንዱ ሀገር ሶስት አመት ኖረህ 

ጸጉርህን ለውጠህ ብትመጣ

ቀድሞም ችግር አይኖርህ

የማን አይን አየህ በክፉ

አንዳችም እንዳትጉላላ ሊያውም ተክነው በዘርፉ

እንደ ሄድክበት ሃገር እረፍትም የሌላቸው

ያንተን ችግር አዳማጭ ክቡር ሚንስትር ናቸው

ምን እንሰይምልህ በየ አደባባዩ

የሚመጡት ልጆች ያንተን ግብር እንዲያዩ

የሚባል ዘመቻ ያለው ላንተ ብቻ

..........ህ.......ም...........

ሽማግሌ ልከህ የከለከሉህን ቆንጆዋን ኮረዳ

በፈለከው ሰአት ስበህ የምትወስደው ከትዬው ጓዳ

በህጻን ባዋቂው እንዲያ ምትወደድ

ብትርቅ አይደልም ወይ ካገር ብት ሰ ደድ!

.......ህ.........ም...........

ታዘብኩት እኔኑ

ታዘብኩት እኔኑ አፈርኩኝ በራሴ

ያን የመሰለ ሃሳብ እንዲያ ማራከሴ

እንኳን በምድራዊው ባለማዊው መድረክ

ለነብስህ ልታድር ልትታረቅ ካምላክ

የላብህን ቋጥረህ ለግዚያር ስጦታ

አስራት ልታወጣ መቀነት ብትፈታ

ካንተ አንድ መቶብር

ያምስት ዶላር ጥሪ ይደምቃል እልልታ

.......ህ.........ም...........

ምን ያደርግልሃል? ምንያደርግልሃል?

ምስጋናቢስ ቄዬ ውለታ ቢስ ሀገር

ለሄደ እየኖረ ያለን ለሚያባርር

ምን ያደርግልሃል? ምን ያደርግልሃል?

ምስጋናቢስ ቄዬ ውለታ ቢስ ሀገር

ለሄደ እየኖረ ያለን ለሚያባርር

......አይ....እኔ......

ጥበበኛ ሲጎል ከያኒ ሲታጣ

ሀገር ነው የሚጎል ቄዬ ነው ሚቀጣ

ባንዲራ ነው ሚፈዝ መዝሙር ቅጥ የሚያጣ

ብዬህ ነበር ያኔ ካገር እንዳትወጣ

አገር፣አድባር የለም ጥበበኛም ጎሏል

ዋርካ ጥላ አይሆንም ሞገስ ክብሩን ጥሏል

የምን ደግሞ ዋርካ

ደግሞ የምን ዋርካ? በደና መጥረቢያ ወገቡ ላይ ሰብሮ

መሬቱን ለልማት ግንዱን ለቤት ማግሮ

ለለውጥ መገስገስ ከተማ አሰማምሮ

ምን ያደርጋል እውቀት አስተሳሰብ ዜሮ!

በድንጋይ ላይ ድንጋይ በህንጻ ላይ ህንጻ

ፋሽኑ ዘንድሮ

ዋሽንግተን ክትፎ ስኩል ኦፍ ፕላኔት

ጀነሬሽን ቢውቲ ፍሪደም ዳቦ ቤት

የጎንደር እስክታ በክለብ አትላንታ

.....ህ......ም.....

ይሄ ነው ትውልድህ አንዳችም ማያተርፍ

ያንተን ባገር መኖር ከቁጥር የማይጥፍ

ስለዚህ.... ስለዚህ....... አጠፍኩት

አትሂድ ያልኩትን ሽሬዋለሁ ዛሬ

ይልቅ ስቴድ ጥራኝ ልሻገር አብሬ

መቼም ያሳ ዝላይ መልሶ ከውሃው ነው

እመጣለሁ ዞሬ፤ስሜን ቀያይሬ

መቼም ያሳ ዝላይ መልሶ ከውሃው ነው

እመጣለሁ ዞሬ፤ስሜን ቀያይሬ

ያኔ ይቀበለኛል ፍቅር ያጠግበኛል

ህዝቤ... ሀገሬ.... ክብሬ

መቼም ያሳ ዝላይ መልሶ ከውሃው ነው

እመጣለሁ ዞሬ፤ስሜን ቀያይሬ

ያኔ ይቀበለኛል ፍቅር ያጠግበኛል

ህዝቤ... ሀገሬ..... ክ.ብ.ሬ


ሜሮን ጌትነት



Monday, February 24, 2025

ሽፍቶችና መሪዎች

መሪዎች ወይም በድንቁርና ወይም በክፋት ወይም በራስ ወዳድነት ወይም በሌላ ምክንያት የተነሳ ወደ ነጂዎች ሲለወጡ ህዝቡ መነዳት ስለሚከፋው ከውስጡ ከአንጀቱ ሽፍቶችን ያፈልቃል ፡፡ እነዚህ ሽፍቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በግልፅም ሆነ በስውር ከህዝቡ ሙሉ ድጋፍ ያገኛሉ ፡፡ ህዝቡ አቀፋቸው ይባላል ፡፡ ስለዚህም ሰነባብተው ሰውተውና ተሰውተው ያሸንፋሉ፡፡ሽፍቶች ነጂዎችን ያስወግዳሉ፡፡ እፎይ ግልግል…… ከዚያስ 

ከዚያማ ሽፍቶች የነበሩ መሪዎች ይሆናሉ- እነሱም ሰነባብተው ለገዛ ምክንያታቸው ወደ ነጂዎች እሰኪለወጡ ድረስ ፡፡ በራሺያ ሰፊ አገር እነ ሌኒን ፣እነ ትሮተስኪ ድንቅ ሽፍቶች ነበሩ፡፡የዓልም አንድ ስድስተኛ ህዝብ በሚኖርባተ በቻይና አገር የተነሱት እነ ማኦ፣ በ ጁ እና ኤን ላይ ተወዳጅ ሽፍቶች ነበሩ፡፡ በቬትናም እነ ሆ ቺ ሚን የሚያስገርሙ ሽፍቶች ነበሩ፡፡ በኩባ እነ ፊደል ካስትሮ ፣እነ ቼ ጉዌቬራ ታይተው ተሰምተው የማይታወቁ፣ዓለምን የነሸጡ ሽፍቶች ነበሩ፡፡ እነዚህ ሁሉ ቆንጅዬ ሽፍቶች የህዝብን ብሶት ይዘው ስለተነሱ ድል አደረጉ፡፡ በሽፍትነታቸው ዘመን ተዓምር ነው ወይም ምትሃት ነው የሚያሰኝ ብዙ ጀብዱ ፈፀሙ ፡፡ የሽፍትነታቸው ዘመን ሲተረክና ሲፃፍ ገድል ይመሰስላል ፡፡ ገድል ነው ደግሞ -ምድራዊ ሆነ እንጅ ፡፡

እንደተለመደው አገርን በሴት ብንመስላት ፣ሽፍቶች የነበሩት ተለውጠው መሪዎች ሲሆኑ ውሽማ የነበረው ሰውዬ ባል ሆነ እንደ ማለት ነው፡፡ሰውየው ያው ሆኖም ፣ በውሽምነቱ ሌላ በባልነቱ ሌላ ፡፡ አረ የትና የት

ባጠቃላይ እንዴው በጭፍን ያህል ስንናገር በአንድ ልብ በአንድ ወኔ ለአንድ ዓላማ ሲዋጉ የነበሩት ሽፍቶች ፣መሪዎች በሆኑ በማግስቱ አላማቸውም ልባቸውም መለያየት ይጀምራል ፡፡ ልዩነቶቻቸው እየበዙ እየከረሩ ሲሄዱ ፣ ጠላትነት እየተንፏቀቀ መሃላቸው ይገባል፡፡በራሺያ ስታሊን ትሮትስኪን ካገር ያባርረዋል ፡፡ከዚያም ሜክሲኮ ድረስ ልኮ ያስገድለዋል ፡፡ሽፍቶች የነበሩት የትሮትስኪ ወገኖች ፣ ሽፍቶች በነበሩት በስታሊን ወገኖች ይጨፈጨፋሉ፡፡

በቻይና ሽፍታ የነበረው ሊዮ ሻዎ ቺ፣ሽፍቶች ወደ መሪዎቹ ሲለወጡ የመከላከያ ሚኒስትር ሆኖ ቆዬ፡፡ ያውም አሪፍ! ተዘርዝሮ የማያልቅ አደጋ አብረው ያሳለፉና ስንትና ስንት ድል አብረው የተቀዳጀጁ ነበሩ ማኦ እና ሊዮ፡፡ በሽፍትነት ዘመን በደጉ ዘመን ፡፡ አለፈቻ የሽፍትነት ዘመን፡፡ አይ ደግ ዘመን ስንትና ስንት አመት የመሞት የመቁሰል አደጋ እያለበትም፣ ረሀብና ውሀ ጥም እየተጠናወተውም አብረን ነበር እምንቆስለው፣ እምንሞተው፣ ባንድ ላይ ነበር እምንራበው ፣እምንጠማው ፣ስናገኝም አብረን ነበር እምንደሰተው ፣ ያውም አንተ ቅደም አንተ ቅደም እየተባባልን፡፡ አይ ውቢቱ የሽፍትነት ዘመን ሁላችንም የህዝባችን ኡኡታ ጠርቶን ወጣን ከየቤታችን ፡፡ ተዋጋነው ያን ኡኡ ያሰኘው የነበረውን (እኛም ህዝብ ነንና የህዝባችን ያካሉ ቁራጭ ነንና የህዝባችንም ኡኡታ ውስጣችንም ነበረ) እና ባንድነት ተዋጋነው -ያኔ ቢያስፈልግ አንተ ለኔ ትሞትልኝ ነበር ፣እኔም ላንተ፡፡ 

ዛሬ ግን ዞረን እኔና አንተ እርስ በርሳችን ልንጋደል ሆነ…በመሀሉ ምን መጣና እንዲሀ ለወጠን? እኔም አንተም እያወቅነው!? ተጋግዘን ጭራቁን ማባረር ሌላ፣ተጋግዘን ቻይናን መምራት ሌላ፡፡ የት ነው የተጠፋፋነው መሰለህ? ሁለታችንም ለቻይና ህዝብ ለመሞት ወይም ለማሸነፍ ወጣን፡፡ በለስ ቀናን አሸነፍን ፡፡ ቀጥሎ ምን መጣ? ያቺን ከህይወታችን አብልጠን እየወደድናት እኩል ልንሞትላት ተስማምተን የተዋጋንላት -ቻይና፡፡

አሁን ተራችን መጣ ፣እንምራት እናታችንን ስንል እኔ በዚህ በኩል ይሻላል ስል አንተ በዚያ በኩል ይሸላል ስትል መንገዳችን ተቃራኒ ሆነ ፡፡ አንተም ከልብህ ካንጀትህ ለቻይናችን ይበጃታል ያልከው -ወደዚያ አመራ፡፡ እኔም ከልቤ ካንጀቴ ለህዝባችን ይሻለዋል ያልሁት ወደዚህ አመራ፡፡ የኔ እና የአንተ አብሮ መጓዝ አበቃ ።

እየወደድኩህ እያከበርኩህም ያንተ መንገድ  ቻይናን ይጎዳታል እንጅ አይበጃትም በዬ ስላመንኩ እቃወማለሁ፡፡ አንተም እንደዚህ ነው ስለእኔና ስለቻይና የምታስበው ፡፡ ምነው ያንተ መንገድ ትክክል በመሰለኝና አብሬህ በተጓዝኩ ባይሆንልኝም ያንተንና የቻይናን መንገድ ለመጥረግ በሞከርኩ፡፡ግን ባንተ ቤት የኔ መንገድ የቻይና ጥፋት በኔ ቤት ያንተ መንገድ የቻይና ጥፋት ፡፡

ቻይና ከመጥፋቷ በፊት ማንም ግለሰብ መጥፋት አለበት- አንተም ሆንክ እኔ፡፡አያሳዝንም?  ወይ እኔ ወይ አንተ መጥፋት ሲኖርብን? እኔና አንተ ልንቻቻል አልቻልንማ! ምናልባት ላንጠፋፋ እንችል ነበር ይሆን? ከኛ በኋላ የሚመጡ አብዮታውያን ያስቡበት፡፡የት እንደተጠፋፋን መርምረው ይደረሱበት፣እዚያ ሲደርሱ እንደኛ እንዳይጠፉ፡፡  

በታሪክ የምናውቃቸው ሊዮ፣ሻዎ፣ቼ እና ማኦ እስከመጋደል ደረሱ ፡፡ ቼ እና ካስትሮ እንደተከባበሩ እንደተዋደዱ ተለያዩ፡፡በታሪክ ሳይሆን በምናባችን ቼ እንዲህ ብሎ ያስባል፡፡በዚህ በኩል ቀድመው ለህዝባቸው የታገሉና ታግለው አሸንፈው በኋላ ‹ቀኝ ኋላ ዙር› ብለው እርስ በርስ የተፋጠጡ አሉ፡፡ በዚህ በኩል ደግሞ የመላው ዓለም ጭቁኖች ብዙ ናቸው ፡፡ የኩባ ህዝብ ትንሽ ነው ፡፡ እናም ነፃ ወጥቷል፡፡ 

በሚቀጥለው ምእራፍ እኔና ፊደል እርስ በርስ መጠራጠር ፣መጠንቀቅ ፣መጠማመድ ፣መገዳደል ከመሚኖርብን ቀድሜ ውልቅ አልለውም? ነፃነት የጠማው ህዝብ መች ጠፋና ሰው እንደሆነ ያው ሰው ነው ፡፡ የትም ቢኖር ምንም ዓይነት መልክ ቢኖረው ፣ ምንም አይነት እምነት ቢኖረው፡፡ ስለዚህ ወደ ቦሊቪያ!

ምናብ ምን ይሳናታል? አሁን ደሞ ፊደል ካስትሮን እንሆናለን ፡፡ በምናብ ፀጋ ያስባል ፡፡ ፊደል ፡፡ ያየዋል ‹ቼ› የጤና ጥበቃ ሚኒስትርም ሆኖ ኩባን ሲመራ ፣የኢንዱስትርም ሆኖ ሲያገለግል፡፡

ገና ይህ ሰውዬ እዚህ ከመምጣቱ በፊት ፣እኛን ነፃ ከማውጣቱ በፊት ፣ በሦስት ሌላ አገር ውስጥ ተዋግቷል ፡፡ አስማውን በአንድ እጁ እያስታመመ ፣ጠላት ላይ በሌላ እጁ እየተኮሰ ፣ ተኩሱ ጋብ ሲል ቁስለኞችን እያከመ፡፡ ያን ሁሉ ጀብዱና ከሞት መፋጠጥ ለምዶ አሁን ኩባን ለማስተዳደር ይቸከዋል፣ይሰለቸዋል፡፡ ምን በወጣው!

በል እንግዲህ ቼ ቢሮክራሲውና ወረቀቱ በቃህ ፡፡ ከእንግዲህ እኛ እንቀጥላለን ፡፡ሂድና ደሞ ሌላ ኩባ ውስጥ ገብተህ ተዋጋ፡፡ ተዋጊ ነህ አስምን በየደቂቃው ትዋጋለህ ብቻህን ምነው አንዲቷን እንኳ በአስም መታፈን እኔ ልታመምልህ በቻልኩ፡፡ሂድ በቃ ተዋጋው ሰይጣንን፡፡ይቅናህ የኔ ጎበዝ ይለውና ይሰነባበታሉ፡፡

ይህ በኩባ ሆነ ፡፡ ወደ ቻይና ስንመለስ ግን ማኦ እና ሊዮ ሻዎ ቺ ተቃቅረው እናገኛቸዋለን ፡፡ነገሮች እየተባባሱ ይሄዳሉ፡፡ አንድ ቀን ሊዮ ሻዎ ቺ ካገር ለመጥፋት በአውሮፕላን ሲበር የሊቀመንበር ማኦ ወገኖች ነቅተውበት ኖሮ ተኩሰው አውሮፕላኑን አጋይተው ይገድሉታል ፡፡ ዘመናት ካለፉ በኋላ  ደግሞ እነ ዴንግ ሲያዎ ፒንግ የሊቀመንበር ማኦን ሚስትና ሦስት ግብረ አበሮቿን ‹‹አራቱ ወንበዴዎች››(ጋንግ ኦቭ ፎር ) በይፋና በብዙ ልፈፋ አዋርደው ያቀርቧቸዋል፡፡

መንግስት በአንድ መልኩ የህዝቡ ጠባቂ ነው ፡፡ ከውጭ ጠላት ይጠብቀዋል፣ እርስ በርሱ እንዳይባላም ይጠብቀዋል፡፡ በሌላ መልኩ ግን መንግስት ምንም ያክል ጥሩ መንግስት ቢሆን አስገዳጅ ኃይል ነው፡፡ለዚህም ፖሊሶች፣ ፍርድ ቤቶች ፣እስር ቤቶች ምስክር ናቸው ፡፡ስለዚህ አንዳንድ ሽፍቶች አሉ፣ ከሽፍትነት በኋላ መሪነቱ የማይጥማቸው ፡፡ከነዚህ እጅግ ዝነኛውና የመላ ዓለም ተራማጆች የሚያመልኩት ጀግናው ቼ ጉዌቬራ ነው ቪቫ ቼ!

ቼ የአብዮታወያን አርአያ ነው ፡፡

‹‹ሀ›› ብልን ስንጀምር የኩባን  ሽፍቶች ወደ ድል ከመሯቸው ቀንደኛ ተዋጊዎች አንዱ የሆነው ቼ ጉዌቬራ ኩባዊ አይደለም ፡፡የአርጅንቲና ሰው ነው፡፡ ‹‹ለ›› ብለን ስንቀጥል ቼ ጉዌቬራ በኩባ ከመከሰቱ በፊት በሦስት ሌሎች የላቲን አሜሪካ አገሮች ውስጥ ከጭቁን ወታደሮች ጋር የተፋፋመ የሽምቅ ዊጊያ ተዋግቷል ፡፡ ኩባ አራተኛ አገሩ ናት ፡፡ በመጨረሻም ኢምፔሪያሊዝምን እየተዋጋ በጀግንነት የወደቀው በአምስተኛ አገሩ በቦሊቪያ ነው ፡፡

ቼ ጉዌቬራ የአብዮታውያን አብዮተዊ ነው ልንል እንችላለን ፡፡አባዛኞቹ አብዮታውያን በትውልድ አገራቸው ውስጥ የገዛ ህዝባቸውን ከጭቆና ነፃ ለማውጣት ነው ሚዋጉት ፡፡ ቼ ግን ሌላ ነው ፡፡የሰውን ልጆች ከጭቆና ለማላቀቅ ነው፡፡ የትም ይሁን የትም ጭቆናን እንዋጋለን! ማንም ይሁን ማንም ጨቋኝን እናወድማለን! ማንም ይሁን ማንም ለጭቁን እንሞታለን!

ቼ ጉዌቬራ አስም ወይም አስማ የሚባለው ትንፋሽን እፍን እፍን የሚያደርገው ፣በሽተኛውን አስጨናቂና የሚያይ የሚሰማውን  ሰው የሚያሳቅቅ በሽታ ፣ ገና በልጅነቱ ተቆራኘው ፡፡በሽታው ከማየሉ የተነሳ ቼ ትምህርት ቤት መግባት አልቻለም ፡፡አስተማሪ ቤቱ እየመጣ ያስተምረው ነበር ፡፡ እንግዲህ ቼ ጉዌቬራ ግማሽ የአልጋ ቁራኛ ፣ግመሽ የቤት እስረኛ ሆኖ ነበር መኖር ያለበት እንጅ ፣ጦር ሜዳ ይሄዳል ብሎ ማን ያስብ ነበር ?

እንግዲያው ምን ለውጥ መጣ? በሽታው ተሻለውን? በጭራሽ ቼ ከበሽታው ጋር እልክ ተያያዘ፡፡ያመኛል እሰቃያለሁ እንጅ በሽተኛ አይደለሁም ፡፡እምቢ በቃ ! በመንፈስ ጥንካሬ ብዛት ነው ቼ ህክምናም የተማረው ፣ጭቆና ላይም የዘመተው ፡፡ አስቸገረ ቼ ጉዌቬራ ላቲን አሜሪካን አመሳት ፡፡ የጭቆናና የብዝበዛ አማልእክትን እንቅልፍ ነሳቸው፡፡ 

ሲ አይ ኤ ተላከ፡፡ቼን በቦሊቪያ ጫካ ከበቡት ፣ገደሉት መልእክታቸው ተሳካ ግን-ቼ ጉዌቬራን ገደልነው ብለው ቢያወሩ ፣ ማንም አያምናቸውም ፡፡ማንም፡፡ ስለዚህ የሬሳውን ፎቶግራፍ አሰራጩ፡፡‹‹ቼ ጉዌቬራ ቅዱስ ነው ››የሚሉ አሉ ባለጥይቱ ቅዱስ ፡፡ እንግዲህ የቼ ጉዌቬራ አምላክ የነፃነት አምላክ አብሮን ይሁን ፡፡ አሜን ፡፡



Monday, January 06, 2025

እኔና ዝናዬ ጨክነናል

ወርኃ ጥቅምት 2017 ዓ.ም መንግሥት አድርጌዋለሁ ያለው 300% የደሞዝ ማሻሻያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው የሚል ዜና በሰማንበት ማግስት ደጉ አከራያችን ሆስፒታል አድሬ ስመለስ ጠብቀው ያዙኝና " ቁርስ በልተህ ቡና ጠጥተህ ተመልስና የማናግርህ ነገር አለኝ " አሉኝ።  የታዘዝኩትን ፈፅሜ ተመለስኩና ለምን እንደፈለጉኝ ስጠይቃቸው ወቅቱን ያማከልና ከጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የቤት ኪራይ ማሻሻያ ለማድረግ መወሰናቸውንና ልጅ አሳዳጊ መሆናቸውን፣ የኑሮ ውድነቱም እየናረ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ በወር 700 ብር ብቻ እንደጨመሩብኝ አረዱኝ።

በተመሳሳይ ቀን እኔና ዝናዬ በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን ከተወያዬን በኋላ ቁርጥ ያለ ውሳኔ ላይ ደረስን። አንበላም አንጠጣም ብለን የገዛናትን  ቤት አዘገጃጅተን ለመግባትና ዶሮ እርባታ ለመጀመር ተስማማን። ውሳኔው ቀላል የሚባል አልነበረም ፤ ጭካኔ ይፈልጋልና ጨክነናል። ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በሯን አስገጥመን፣ ውስጧን አስለስነን፣አጥሯንም በቆርቆሮ አሳጥረን በእለተ ሐሙስ ህዳር 12/2017 ዓ.ም (የህዳር ሚካኤል እለት )እቃችን ጠቅለለን ወደ ቤታችን ገባን። የቤት መግዣውን ሳይጨምር ውስጧን ለማስለሰን 16000 ብር፣በርና መስኮት በላሜራ ለማሰራት 17000 ብር፣ አጥሯን በቆርቆሮ ለማሳጠር 24000 ብር በድምሩ 57000 ብር ጨርሶብናል።

ይህን ለማድረግ ደግሞ ወደፊት የግል ክሊኒክ ለመክፈት የገዛሁትን centrifuge(15000 ብር ), autoclave(15000 ብር ), examination bed(6500 ብር),  ፍሪጅ(25000 ብር ተገዝቶ 18000 ብር የተሸጠ)፣ እንዲሁም ለማንበቢያ የገዛኋትና እንደ ዓይኔ ብሌን የምወዳትን Tablet(9000 ብር) መሸጥ ነበረብኝና ሽጥኩ። መጨከን ነበረብኛ!
ዶሮ እርባታውን ለመጀመር ግን ጨክኖ መነሻ በጀቱን የሚሸፍንልን sponsor እንፈልጋለን።
አስቻይ ሁኔታዎች
1ኛ የተመቻቸና በቂ ቦታ ያለን መሆኑ
2ኛ. ቀዳማዊት እመቤቷ ( ወ/ሮ ዝናሽ መኬ ) የተመሰከረላቸው የዶሮ እርባታ expert መሆናቸው
3ኛ. የጠቅላዩ ዶሮ እርባታን የሚያበረታታ አቋም

በጀት
የቄብ ዶሮ መግዣ: 100*300=30,000
የዶሮ ቤት መስሪያ: 10,000-15,000
የቄብ መኖ 5 ኩንታል*5000ብር =25000
መመገቢያ 4*300= 1200
መጠጫ :2700
የእንቁላል መጣያ ሳጥን: 1500
የእንቁቃል መሰብሰቢያ: 270
አካፋና መዶሻ :2*500=1000
ሳፋ :2*400=800
ፕላስቲክ ባሊ:2*200=400
ለውኃ ማስገቢያ :10,000-15,000
ሮቶ :2000
ለክትባትና መድኃኒቶች(H2O2ና ሳሙናን ጨምሮ) :5000-7000
ሌሎች ወጪዎች 15000-20000

ጠቅላላ ድምር 80000-120000

እኔና ዝናዬ ጨክነናል!
ዝናሽ የዶሮ እርባታ  ማእከል እውን ይሆናል።

19 ዓመት ተምሮ ለምድር ለሰማይ የሚከብድ ማእረግ እንደተጫነበት አንድ ኢትዮጵያዊ ሀኪም ይህን ጦማር ይዞ  ማህበራዊ ሚዲያ ላይ መውጣት በራሱ ሌላ ከፍ ያለ ጭካኔ ይጠይቃል።
ገረማችሁ አይደል። አትገረሙ ደግሞም አትሰስቱ ። ይልቁንም የአቅማችሁን ጠጠር ወርውሩ  ፤ repost በማድረግም ለሚመለከታቸው አጋር አካላት አድረሱልን።
ስልክ:+251918666678/+251962443989
BOA Acct: 212465933
                      ZINAYE MEKIE YITAYH
CBE Acct: 1000316337949
                     Getaneh Kassie Gashu

https://lnkd.in/gjmvvQ4h




Wednesday, September 04, 2024

በልብስ ወበሢሳይ ኢታርእዪኒ ንዴተ

 በልብስ ወበሢሳይ ኢታርእዪኒ ንዴተ

እስመ ቁር ወረኃብ ያረስእ ጥበባተ
በአፄ ምኒልክ ዘመን አለቃ ተክሌ የሚባል የንጉሥ ተክለኃይማኖት አሽከር በአፈ ንጉሥ ይግዛው ስም የተንኮል ማህተም ቀርጠኻል በሚል ተወንጅሎ እስር ይፈረድበታል። ወህኒ ቤት በገባ ጊዜም "ስለ እግዚአብሔር ብለው አይርሱኝ፤ ለጃንሆይ ያስተዛዝኑልኝ፤ ዘመድ የለኝም"ብሎ አሳላፊ ውቤን ወደ እጨጌ ወልጊዮርጊስ ላከ። አለቃ ተክሌ ወህኒ ቤት ሳለ መልክአ ኤዶም ይደግም ነበረ። ያን ጊዜም ከበጅሮንድ ገድሌ ቤት ታሥሮ የተቀመጠው አለቃ ተገኝ "ወረድኦ ለነዳይ በተጽናሰ (ችግረኛውን በችግሩ ጊዜ ረዳው)" የሚል ሕልም ስለ አለቃ ተክሌ አየ።
አለቃ ተክሌ መልክአ ኤዶም እየደገመ ባዘነበት የሰኔ ማርያም እለት እጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ ለእቴጌ ጣይቱ ነገረለት። እቴጌ ጣይቱም "ለጃንሆይ ነግሬ አስፈታዋለሁ፤ ጉራምባ ማርያምን ይሥልልኛል" አለች። ከዚያም " አለቃ ተክሌን ፈተው ለእኔ ይስጡኝ፤ ጉራምባን ይሣልልኝ፤ በሎልነቱ ታዝዞ ማኅተም ቢሰራ በርሱ ምን ኃጢአት አለበት ?" አለችና ለጃንሆይ ተናገረች። እጨጌ ወልደጊዮርጊስም አከታትሎ አስተዛዘነለት ።አፄ ምኒልክም "እሽ ይፈታ" አለ።
ለአማኑኤል ተስሎ ቀሚሱን በሰጠበት ሰኔ ፳፰ ቀን የአማኑኤል ዕለት ከወህኒ ቤት ወጣ። ከተፈታ በኋላ ለእቴጌ ሹም ለአዛዥ
ዘአማኑኤል ተላለፈ። አዛዥ ዘአማኑኤልም ራት ምሣውን፣ ምንጣፍ ሥፍራውን አዘዘለትና በማዕረግ ተቀመጠ። ነሐሴ ፪ ቀን እቴጌ ጣይቱ ሙያውን ልትሰልል "ሥዕለ ማርያም በወረቀት ሥለህ ስደድልኝ" ብላ ላከችበት። እርሱም ፩ ሉክ ወረቀት ተቀብሎ ጥሩ ሥዕል ሥሎ ከሥዕሉ ግርጌ
ኢትኀድግኒ ዓቂበ
በልብስ ወበሢሳይ ኢታርእዪኒ ንዴተ
እስመ ቁር ወረኃብ ያረስእ ጥበባተ
[መጠበቅን አትተይኝ
በልብስና በምግብ ችግር አታሳይኝ። ብርድና ረሃብ ጥበብን ያስረሳልና።] የሚል ጽሑፍ ጽፎ ሰደደላት።
እቴጌ ጣይቱም ሥዕሉን አይታ አደነቀች ፤ለጃንሆይም አሳየች ። ከሥዕሉ ግርጌ ያለውን ጽሑፍ ባየች ጊዜ አዛዥ ዘአማኑኤልን ተቆጣች። "ካላስራብኸው እንዲህ ብሎ አይልክም" አለች። አዛዥ ዘአማኑኤልም ከመጣ እስከ ዛሬ ድርጎው አልገደለበትም። "እንዲያው ጎጃሞች ልፍ(ማሳጣት፣ክስ) ይወዳሉ "አለና አለቃ ተክሌን ተጣላው። እቴጌ ጣይቱ ግን የሰርክ ልብስ፣የሌሊት ቡልኮ፣ ለቀን ጥበብ ኩታ፣ እጀ ጠባብና ሱሪ በርኖስ ዳረገችው። ነሐሴ ሲያልቅ ጳጉሜ ፫ ቀን ጉራምባን ይሣል ብላ ፫ ዳውላ እህል ቀለብ፣ ፪ ጉንዶ ማር፣ ለወር ፩ ሙክት፣ ለ ፲ ቀን ፭ ኩባያ አሻቦ፣ ፩ እቃ ቅቤ፣ ጾም ቢሆን ቅባኑግ ለወር ዳረገችው። የቀለም መበጥበጫ ፲፪ ፍንጃል አዘዘች።
ኢትኀድጉኒ ዓቂበ
በልብስ ወበሢሳይ ኢታርእዩኒ ንዴተ
እስመ ቁር ወረኃብ ያረስእ ጥበባተ
[መጠበቅን አትተውኝ
በልብስና በምግብ ችግር አታሳዩኝ። ብርድና ረሃብ ጥበብን ያስረሳልና።]


ፍኖተሰላም ሆስፒታልን ከልጅነቴ ጀምሮ አውቀዋለሁ።




ፍኖተሰላም ሆስፒታልን ከልጅነቴ ጀምሮ አውቀዋለሁ።

የታመመ ሰው ህክምና ለማግኘት ጥዋት 11 ሰዓት ላይ ከሆስፒታሉ ግቢ ውጭ ነበር ወረፋ የሚይዘው (ይሰለፋል)። ወይም ወረፋ ከሚይዙ ወጣቶች መግዛት ይጠበቅበታል (ከተሜ ከሆንህ ነው)።
እድለኛ ከሆነና ከውራጌወች ካመለጠ ፣ ከብዙ ስቃይ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዲገባ ይፈቀድለታል። እድለቢስ ከሆነ ደግሞ በተረገሙ ውራጌወች ተደብድቦ ገንዘቡንና ስንቁን ይቀማል (ህክምና ሲመጣ ስንቅ ተይዞ ነበር የሚመጣው ቢያንስ ለሳምንት የሚሆን፣ ክብ ዳቦ፣ ዳቦ ቆሎ፣ በሶ)። አልያም ለቀጣይ ቀን ይቀጠራል።
ከሆስፒታሉ አጥር ውስጥ ሳይገባም ህይወቱ የሚያልፍ ብዙ ታካሚ ነበረ። ሀኪም አግኝቶ ታክሞ ከተሻለው ፣ ተንበርክኮ መሬት ስሞ ፣ አገር ይባረክ ፣ ወንዝ ይባረክ፣ አገራችን ኢትዮጽያን ይጠብቅልን፣ ገበያውን ጥጋብ ያርገው፣ በእውቀት ላይ እውቀት ደርቦ ይስጥህ ብሎ ከልቡ መርቆ ይሄዳል።
ካልተሳካ ደግሞ ወደ ባህርዳር ወይም ደብረማርቆስ ሪፈር የሚባለው ታካሚ በጣም ብዙ ነበር (ወደ ከፍተኛ ተብሏል ፣ ግልኮስ ተደርጎበታል፣ ህመሙ ሳይጠናበት አልቀረም፣ ኧረ እኔስ ፈርቻለሁ አይመለስም ፣ይባል ነበር) ።
ያን ሁሉ መከራ ግን ዛሬም አልቀረም ፣ ብዙ ነገሮች በተሻሻሉበት ዘመን ፣ ወንበር ላይ ተቀምጦ ኦክስጅን ይወስዳል፣ ፈጥኖ የመጣና እድለኛ ከሆነ ደግሞ የጎኑ ማሳረፊያ ደረቅ ወንበር ያገኛል፣ አልያም ፍሳሽ የሚወርድበት ክፍል ውስጥ የዛገ አልጋ ላይ ጣል የተደረገች ብል የበላት ፍራሽ ትሰጠዋለች።
አካባቢው የተማሩ ልጆች እያሉት፣ እያመረተና እየገበረ ምን ስላደረገ ነው ይህ ማህበረሰብ በዚህ ልክ የሚሰቃየው! ተማርን የምንል ሰዎች፣ ነጋዴዎች እና ባለስልጣናት የማህበረሰቡ ህመም ሊያመን ይገባል።
ለዚሁ ዓላማ ብቻ የተከፈተውን የ telegram group ይቀላቀሉ።
NB: "ውራጌ" ማለት በአካባቢው ዘዬ ሌባ ፣ ነጣቂ ፣ ቀማኛ፣ ዘራፊ ማለት ነው
ዶ/ር የሮም ጌታቸው የፍ/ሰላም ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር

ኑ! ሆስፒታሉን ሆስፒታል እናስመስል

ግርማዊነታቸው ከጣሊያን ጦርነት በኋላ ከስደት ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የጎጃም እምብርት ላይ በምትገኝና ወጀት ተብላ በምትጠራ ትንሽዬ ከተማ ላይ ከአጃቢዎቻቸው ጋር እረፍት ያደርጋሉ። እስከዚያን ጊዜ ድረስ ያደረጉት ጉዞ በሰላም የተሞላ ነበርና ከተማዋን ፍኖተ ሰላም ብለው ሰየሟት። የሰላም መንገድ ማለታቸው ነው፡፡ ከከተማዋ ወጣ ብለውም ለማስታወሻ ይሆን ዘንድ አንድ ዋርካ ተከሉ።

ጃንሆይ በቆይታቸው ሰው ሰው አክባሪ፤ወዲህ እንግዳ ተቀባይ፤ አካባቢው ጤፍ፣ በቆሎ፣ ዳጉሳ፣ ኑግ፣ በርበሬ እና ሌሎችንም የእህል አይነቶች የሚያበቅል፤ ሎሚ፣ ብርቱካንና ፓፓዬ እንደልብ የሚግኝበት፤ በተፈጥሮ ለምነትን የታደለ፤ መሆኑን አስተዋሉ። የባከልን ቡና ቀምሰውም በጣዕሙ ተደመሙ። ጃንሆይ ምልከታቸው በዚህ አላበቃም፡፡ የአካባቢው ህዝብ በስጋ ደዌና በቲቪ በሽታ እንደሚሰቃይ አይተው አውጥተውና አውርደው ሆስፒታል አስገነቡለት፡፡
ከ62 ዓመታት በፊት ቲቢና ስጋ ደዌ በሽታን ለማከም ታስቦና አብዛኛው ወጪው በህዝቡ ተሸፍኖ የተገነባው ፍ/ሠላም ሆስፒታል በ1976 ዓ.ም በከፍተኛ የአካባቢዉ ማህበረሰብ ተሳትፎ ማስፋፊያ ተደርጎለት በገጠር ሆስፒታል ደረጃ ለማደግ የቻለ ሲሆን፤ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ጠቅላላ ሆስፒታልነት በክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ ለማደግ ችሏል፡፡ ተቋሙ 297 የጤና ባለሟያዎች እና 102 የአስተዳደር ሰራተኞች በድምሩ 399 ቋሚ ተቀጣሪ ሰራተኞችን ይዞ ለአካባቢው ማህብረሰብ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይግኛል፡፡
በ2016 ዓ.ም 88,230 የተመላላሽ ታካሚዎችን ፣5,704 ተኝቶ ታካሚዎችን ፣ 11,462 የድንገተኛ ክፍል ታካሚዎችን፣3,479 የወሊድ አገልግሎት፣1,754 ከፍተኛ ቀዶ ጥገና ስራዎችን እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የሆስፒታል አገልግሎቶችን ሲሰጥ የከረመ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በቀን 400-600 ህሙማንን እያስተናገደ ይገኛል፡፡ ሆስፒታሉ በስሩ አምስት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ማለትም( ፈረስ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ደምበጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ፣ቡሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ፣ዱርቤቴ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ፣ሊበን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል) እንዲሁም ሶስት የከተማ ጤና ጣቢያዎችን( ቋሪት ጤና አጠባበቅ ጣቢያ፣ ጅጋ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ፣ፍ/ ሰላም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ) በስሩ በክላትተር ትስስር ይዞ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጅ ይህ የእድሜ ባለጸጋ ሆስፒታል ከአቻዎቹ ጋር እኩል ማደግና ዘመኑን የዋጀ እንዲሁም ያለውን የታካሚ ፍሰት የሚመጥን አገልግሎት መስጠት ባለመቻሉ በተደጋጋሚ ቅሬታዎች ይነሱበታል። በቅርቡ ባዲስ መልክ የተዋቀረው የሆስፒታሉ ማኔጅመንት ይህንን ችግር ለመፍታት ኮሚቴ አቋቁሞ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ኮሚቴውም ሆስፒታሉ የሚጠበቅበትን አገልግሎት በአግባቡ እንዳይሰጥ ማነቆ የሆኑበትን ችግሮች በመለዬት እንደ ችግሩ ስፋትና ክፋት በቅደም ተከተል ለመፍታት ደፋ ቀና በማለት ላይ ነው፡፡
ስለሆነም የፍኖተሰላም ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች፣ተወልጆች፣ባልሃብቶች፣አዋቂና ታዋቂ ሰዎች፣የሚመለከታችሁ የመንግስት አካላት፣መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆናችሁ ድርጅቶች ሆስፒታሉን ሆስፒታል ለማስምሰል በምናደርገው እንቅስቃሴ ሁሉ ተቋሙን እንደ ራሳችሁ ቤት ቆጥራችሁ ከጎናችን እንድትቆሙ ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ለዚሁ ዓላማ ብቻ የተከፈተውን የtelegram group ይቀላቀሉ


Sunday, May 17, 2020

"We need our limited health resources for things which are actually killing us"

We are chasing COVID 19 off a cliff.
The majority of our population, who don't already seek modern medical care are now even more afraid to visit hospitals. For this reason work at hospitals has slowed down.

Health education given about COVID 19 doesn't seem balanced based. Based on the world population review, in our country 1984 peoples die every day and a big chunk of that number is by medical reason. Remember why we let RVI +ve mothers to breast feed, inspite of clear CDC recommendation that "the best way to prevent MTCT through breast milk is not to breastfeed" We  rather take the risk with the RVI than the malnutrition. We should apply the same principles in this scenario.

Let me refer the EDHS 2016 and mention the areas which will be affected more by the decreased patient flow. In Ethiopia, 73% births occur at home with a high maternal mortality rate of 412/100,000 live births and  81 % don't recieve any  postnatal care. "According to Health data .org neonatal disorders are the number one causes of death in Ethiopia". Back to EDHS, the basic vaccination coverage for all eight basic vaccines is 40 % .

You know there isn't much recent data about our morbidities but let's take a report by "world life expectancy" to have a general picture. Diarrheal diseases account for 8% of deaths in Ethiopia, 3.81% are due to Tuberculosis, 7.38% are due to Coronary Heart disease, 3.21 l are due to HIV, stroke 6.23% , cirrhosis 2.24% and meningitis 2.8%. If we consider the world population review report of 1984 death per day in Ethiopia. We will have rough estimation of our disease burden.
©Dr.Kirubel Tesfaye