Tuesday, April 26, 2016

ሀቁን ካንቺ ልስማ

ሰላም ላንቺ ይሁን ለንጽህት እናቴ
ሳዝን መጽናኛየ ስደክም ብርታቴ፣
የመኖሬ ምስጢር የህይወቴ አንድምታ፣
ከሰማይ የተላክሽ የንጉሥ ስጦታ ፣
አማናዊት መርከብ ምሥለ ጎልጎታ፣
የሸክሜ ማቅለያ የምስጢር ዋሻዬ፣
ከጭንቀት ማምለጫ ጥላ ከለላዬ፣
ሰላም ላንቺ ይሁን ሰላም ነሽ እማዬ?
የምነግርሽ አለኝ ጆሮ ስጭኝ እማ!
እኒያ ጡት ነካሾች ሲሰድቡሽ ብሰማ፣
ውስጤ ተቃጠለ ሕሊናዬ ደማ፣
እውነቱን ንገሪኝ ሀቁን ካንቺ ልስማ፤
እውነቱን ንገሪኝ ሀቁን ካንቺ ልስማ።
ምን ጥፋት ሰርተሽ ነው? ምን በድለሻቸው?
አሻግረው ስላዩሽ ሚያንገሸግሻቸው።
ቆይ ምን ብተሰሪ ነው?
እኮ ምን ሰርተሽ ነው? ምንድን ነው ነገሩ?
እናጠፋታለን ብለው ሚፎክሩ።
ለምስጢር ያልበቃሁ ብሆንም ጎስቋላ፣
ትዕዛዝሽን ያልጠበቅሁ አደራ ምበላ፣
አፈር ትቢያም ብሆን ቢበዛም ሀጢአቴ፣
ቃላት መገጣጠም ባይችል አንደበቴ፣
እውነቱን ልወቀው ንገሪኝ እናቴ፤
እውነቱን ልወቀው ንገሪኝ እናቴ።

No comments:

Post a Comment