Thursday, June 29, 2017

💌መርዶ💌

Love joy and peace are deep state of being..........as such they have no opposite. This is because they arise from beyond the mind. Accordingly real love doesn't make you suffer. How could it ? It doesn't suddenly turn into hate,nor does real joy turn into pain .

The reason why many love relationships after the initial euphoria  passes,or  oscillate between "love" and hate,attraction and attack, is that what we usually call love is the short lived pleasurable  aspect of  emotion which is subject to the law of opposites; which states every thing that gives you pleasure today will give you pain tomorrow,or it will leave you,its absence will give you pain. . . . . . {the power of now}

ከዩኒቨርሲቲ መመረቅን ምክንያት በማድረግ “ስለነበረን ጊዜ አመሰግናለሁ።” የሚል መልእክት ((መርዶ)) የደረሳችሁ ወይም ለመባል በዝግጅት ላይ ያላችሁ “አፍቃሪያን” መፅናናትን ከአርያም ይልክላችሁ ዘንድ እመኝላችኋለሁ።አንዳንዶች የገንዘብና የዝሙት ጥማታቸውን አወንታዊ ገጽታ በተላበሰ  መልኩ ለማርገብ ሲፈልጉ “ፍቅር” የሚል ስም ይሰጡታል። ታዲያ ይህን ድብቅ ጥማታቸውን የሚያስታግስ የተሻለ  አማራጭ ሲያገኙ የቀደመ ፍቅራቸው በጥላቻ፣ መውደዳቸውም  በንቀትና በኩራት ይተካል።

እውነተኛ ፍቅር ግን እየተጠሉ መውደድ፤እየተካዱም ማመን ነው። እውነተኛ ፍቅር ይታገሳል ፤ ቸርነትንም ያደርጋል እንጂ አይቀናም ፤አይታበይም ፤የማይገባውን አያደርግም ፤በደልን አይቆጥርም። እውነተኛ ፍቅር ማለት የሚወዱትን ሰው አስገድዶ የራስ ማድረግ ወይም የራስን ፈቃድ ማስፈፀም ሳይሆን የተወዳጁንም ምርጫና ፍላጎት ማክበር ነው። 

ሳንጠይቀው ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረንና  አንድያ  ልጁን ለሞት አሳልፎ እስኪሰጥ ድረስ እንዲሁ የወደደን እግዚአብሔር እንኳን “እኔ የፈጠርሁትን  አየርና ውኃ፣ ፀሐይና መሬት እየተጠቀማችሁ፤ የበደላችሁንም ካሳ ከፍዬ ከኀጢአት ባርነት ነጻ አውጥቻችሁ፤ እኔን ከመውደድ (ከማምለክ) ውጪ ሌላ አማራጭ የላችሁም” አላለንም። የእውነተኛ ፍቅር መገለጫው ይህ አይደለምና።  ((©ጌች ቀጭኑ))

Tuesday, June 13, 2017

congratulation !!!

My respected colleagues; Dear Bulcha Nuguse, Dear Behailu Bizuneh and Dear Endalaye Mulugeta the president, vise president and secretary respectively of jimma university students union in the upcoming year 2010 E.C; First of all I would like to say congratulation  for winning the election held in our campus last sunday. Saying this I would like you to bear in mind the following short and presize message so that you will be the best  leaders ever seen in the union.

A leader takes people where they want to go. A great leader takes people where they don’t necessarily want to go, but where they ought to be. Leadership does not always have to come from a position of authority. "If your actions inspire others to dream more, learn more,do more, and become more, you are a leader"John Quincy Adams. A key characteristic of all great leaders is the willingness to serve as the leader.

Wednesday, June 07, 2017

⛅ሙሉዋ ጨረቃ⛅

ሙሉዋ ጨረቃ
ብሩህ ነሽ ደማቃ
ታለቅሳለች ነብሴ ተስፋ ትቆርጥና፣
በውበትሽ ተማርካ በመራቅሽ አዝና።
ብሆን ከወለሉ አንቺም ጣሪያ ላይ
ዝቅዝቅ ከሚያዩትስ እሚያምር የለም ወይ?
አንገትን ሲያቀኑ ብቻ ነው ማማሩ፣
ያም ይሄም ያም ይሄም ዐይንን ማጭበርበሩ፣
ፈክቶ መታየቱ ሽልምልም ማለቱ
በሩቅ ማጓጓቱ?
ለዓይንም ሌላ  ዓይን አለው
-አንድን ጥርኝ አፈር-
ድንጋይ ብሎ እሚያስጥል በየጉራንጉሩ፤
ወርቅ ብሎ እሚያስቋጥር በየማህደሩ፤
እኔውም  ብሆን ነው የዓይኔ ዐይን ባርያ፣
ሳውቀው መሆንሽን የሌሎች አምሳያ፣
ጉልላት ያረኩሽ የፍጥረት እናት፣
በውን እምትሞቂ ድንቅ የሕልም እሳት።
ዳኛ ነው የሚፈርድ ምክንያት ጠቅሶ መጽሐፍ አንብቦ
ግን ከሳሽ ተከሳሽ/ያው እንደኔ እንዳንቺው/
ስሜቱን አንግቦ
አእምሮው ረግቦ
አውቃለሁ እንዳይሻር ይህ ብሉይ አዋጅ፣
ከአለኝታዬ አይጃጅ በምኞቴ አይዋጅ፣
እንደነበር ሲኖር መታከት መታከት
መታከት ነው እንጅ።
ነውናም ስገብር ለዐዋጁ ለዕጣዬ፣
አንቺ ዝቅ ብለሽ ወይ እኔ ከፍ ብዬ፣
እንገናኝ ይሆን? ሆኗል ጥያቄዬ።

ምንጭ ፦ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ
            በደበበ ሰይፉ

Tuesday, June 06, 2017

የማስቲካ እድሜ ስንት ነው?

ባለፈው ቅዳሜ ዕለት ወደ መርካቶ ((የጅማዋን መርካቶ ማለቴ ነው)) እየሄድኩኝ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ሁለት የግቢያችን ሴት ተማሪዎች እኔ የተሳፈርኩበት ታክሲ ውስጥ ከኋላዬ ተቀምጠው ነበር ። ልጆቹን በደንብ አላውቃቸውም ከግቢው በር ወጥተው እኔ ካለሁባት ታክሲ እስከሚገቡ ድረስ እንደከለምኳቸው ከሆነ  ግን አንዲቱ ጠይምና ወፈርፈር ያለች ቁጥር  መልኳ የኔ ቢጤ አፍንጫ ጎራዳ ስትሆን ትክሻዋ ላይ የተዘናፈለው የተፈተለ ሐር የመሰለ ፀጉሯ ቀልብን የመሳብ መግነጢሳዊ ኃይል አጎናፅፏታል። አንደኛዋ ደግሞ ቀላ ያለችና የደም ገንቦ ናት ለማለት ባታስደፍርም የደስደስ ያላት ልጅ ነች።((ከጉልበቱ ላይ የተቀደደ ሱሪ ከመልበሷ በቀር))። 

ልጆቹ ከብዙ ተሳፋሪዎች  ጋር ከቆጪ ወደ መርካቶ የሚሄዱ ሳይሆን በሌላ ዓለም ውስጥ የራሳቸውን ክፍለ ሀገር ፈጥረው የራሳቸውን ህይወት የሚኖሩ ይመስላሉ። የእኛን ታክሲዋ ውስጥ መኖር አለመኖር ከምንም ቆጥረው የመጣላቸውን ሁሉ ያወራሉ። ወዲያው ገብተው ከኋላዬ እንደተቀመጡ “አንደኛዋ  ማስቲካ ከየት አመጣሽ?” አለች ጮህ ብላ። “የቅድሙ ነዋ” አለች ሌላኛዋ በአፏ የያዘችውን ማስቲካ ጧ! ጧ! እያደረገች። “የጥዋቱን እስካሁን እያኘክሽ ባልሆነ” ጥያቄዋን ቀጠለች።“አወና” በማለት መለሰችላት ቀብረር ሞልቀቅ ባለ አነጋግር። “ኧረ ይቅር ይበልሽ እኔ አንድ ማስቲካ ከሁለት ሰዓት በላይ ማኘክ በጣም ነው ሚያስጠላኝ እሽ! አንቺ ደግሞ እየለጠፍሽ ነው እንዴ  ድጋሜ ምታኝኪው?”((እየለጠፉ ማኘክ የሚሉትን ነገር አላረፍሁትም )) ።

Friday, June 02, 2017

💘💘 ታሚኛለሽ አሉ 💘💘

ይወደኛል ብለሽ ታሚኛለሽ አሉ፣
ለወጭ ለወራጁ ለሳር ለቅጠሉ።
እርጥብ በሚያቃጥል የፍቅሬ ነበልባል፣
መሰንበቱን እንጃ እጅጉን ተጎድቷል፣
እንደፊቱም አይደል ከሰውነት ወጥቷል፣
ቀልቡን ብቻ ሳይሆን ልቡናውን አጥቷል፤
እያልሽ በየሜዳው ሟርት ከምትዘሪ፣
የልብ ጆሮ ግዥ ቆንጂት ተመከሪ፤
ወደ አንቺ ተመልከች ውስጥሽን መርምሪ፣
በዝሙት ያደፈ ህሊናሽን አጥሪ።
“ለምን?” አትይኝም?
“ለምን?” ማለት ጥሩ!
ከቧልትሽ ገበታ የታደሙ ሁሉ፣
ሲያሙሽ ታዝቢያለሁ ሥጋሽን ሲበሉ፣
ደጅ ለመታው ሁሉ ከፈተች እያሉ።
*ጌች ቀጭኑ ከገዳም ሰፈር: ግንቦት 22/2009 ዓ.ም*