Saturday, February 18, 2017

ዘመናዊት ጀግና

ከሰማይ ዶፍ ቢወርድ ቢዘንብ መከራ፣
ጠላት ቢያንገራግር ቢፎክር ቢያቅራራ፣
ችግር ቢደራረብ ቢመስል ተራራ፣
ጠብ የሚል ባይገኝ  ከምድር ጎተራ፣
ከአቋሟ የማትወርድ ልቧ የማይፈራ፤
በእምነቷ የጸናች ቃሏ የታመነ፣
ክብሯ ከነገሥታት ልጆች የገነነ፤
በሐሜት በወሬ ልቧ 'ማይሸበር፣
በሰው መጠቋቆም ቅስሟ 'ማይሰበር፣
ነገን የምትጨብጥ ዛሬን ተረግጣ፣
ዘመናዊት ጀግና አብቅሏል ሰቆጣ።

No comments:

Post a Comment