Tuesday, June 02, 2015

ገንዘብ

10624745_1730988887125730_7825557555215847685_n
ፍሬ መሬት ወድቆ ከዋለ ካደረ፣
ገንዘብ ሰውን ገዝቶ መቅበር ከጀመረ፤
የመጣ ነውና ቀድሞውን ከጥንት፣
ሁለቱም አይድኑም ከመበላሸት፤
ገንዘብ መፈጠሩ ለሰው አገልጋይ፤
ሆኖ ሊሰራበት አልነበረም ወይ?
አሁን ግን መስገብገብ በጣም ስለበዛ፣
ሰው ባሪያ እየሆነ ለገንዘብ ተገዛ።
ለስሙ ስም አለን ከጥንት እስከ አሁን፣
በእምነታችን ኗሪ ሟች ለክብራችን፣
በማጣት ተወልደን በንጣት አድገን፣
ለገንዘብ እጅ ሰጠ ኩሩልባችን።

No comments:

Post a Comment