Tuesday, May 05, 2020

አላቲኖስ



የፊስአልጎስ ሕቡዕ  የመሰብሰቢያ አዳራሽ በዝምታ አርምሞ ተመቷል።ብዙዎች የገመዳ ውሳኔ ያልጠበቁት የማይታመን ሆኖባቸዋል ።ገመዳ ብዙ ሰላማያወራ ብዙም ስለማንነቱ እንዳያውቁ ስላደረጋቸው መደነቅን ፈጥሮባቸዋል ።

የመሰብሰቢያ አዳራሹን ፀጥታ “አይሆንም”የሚለው የታንቱ ንግግር አደፈረሰው ።”…ይህማ አይሆንም ምን ማለት ነው ?ለምንድነው ለልጆችህ ሰቀቀን የምትሆነው ?ስለምንድነው ይህን የሚያክል ሃላፊነት ትተህ ራስህን ለመከራ የምትዳርገው ?ባይሆን እኔ ሕይወትን ያልጀመርኩት ሐላፊነቱን እወስዳለሁ እንጅ እንዴት ነው አንተ የምትማገደው?”አለ ታንቱ እንባ እየተናነቀው ።

ሐዊ ክው ብላ ደንግጣለች ።ስለደነገጠች ነው መሰል ጉንጯ መሰርጎዱን ያቆመ ይመስላል።በታንቱና በገመዳ ፍቅር ፤ከምንም በላይ ለቤተ ክርስቲያን ሕይወታቸውን ለመስጠት ያላቸውን ቁርጠኝነት ስታይ ደነገጠች ።ክርስትና ከዚህም  በላይ ዋጋ እንደሚያስከፍል በታሪክ ከቅዱሳን መጽሐፍት ብታነብም እንዲህ በዓይኗ ግን ‘እኔ ልሰዋ እኔ ልሰዋ ‘ሲባል አላየችም አልሰማችም።

አበጋዝም ይህ ፍቅር አስደግጦታል።ሌሎች የሥራ አስፈጻሚ አባላትም  የሚናገሩትን ቃላት አጡ።አብጋዝ ግን እንደ ምንም ልውጣ አልውጣ የሚለውን እንባውን አምቆ መናገር ጀመረ ።”እናንተ ምን በወጣችሁ ነው ዋጋ የምትከፍሉት ያወራሁት እኔ ፤የሰበክሁት እኔ፤የደሰኮርኩት እኔ፤ እንዴት ተደርጎ ነው እኔ እያለሁ እናንትነ ሃላፊነት የምትወስዱት ?”

“አይሆንም”አለ ታንቱ በድጋሜ።ሁሌም እንደሚያደርገው መሃል አናቱን ቆፈር ቆፈር አደረገና”አይሆንም ምክንያቱም ብዙ ሰዎች አንተን የማህበረ ቅዱሳን አባል ነው የሚያድርጉህ፤ ስለዚህ አንተ እኔ ነኝ ብትል ለማህበሩ ሌላ መከራ ትጠራለህ እንጅ የምታመጣው ለውጥ የለም።ትርጉም የለሽ መስዋዕትነት ደግሞ አንከፍልም ።የምንከፍለው መስዋዕትነት ደግሞ በምድርም በሰማይም በረከት ቢያመጣልን መልካም ነው ።ሲቀጥል ትናንት አውደምህረት ላይ ሰብከህ ዛሬ ገዳይ ብትባል አሁንም ለቤተክርስቲያናችን ውርደት ነው ።እኛ የማንታወቀው ግን ምንም ችግር የለውም ።”የመሰብሰቢያ ክፍሉ ለጥቂት ሰከንድ ፀጥ አለ።

ዝምታውን ለመስበር ያህል ገመዳ ንግግሩን ዳግም ጀመረ ።”ሁላችንም መስዋዕትነት ለመክፈል የሚያስቸኩለን አይመስለኝም።ዘመኑ ዋጋ ይጥይቃል ስለዚህ ብንቀዳደም እንጅ መስዋዕትነቱ እንደሆነ ለእያንዳንዳችሁ አይቀርላችሁም። ስለዚህ እንደፊስአልጎስ ሰብሳቢነትም ቅድሚያ ሐላፊነቱን ልወስድ ግድ ነው ።ከከራድዮን ወፍ የምንማረው ይህንኑ ነው ።በዚያ ላይ ናፍያድን አውቀዋለሁ።ዩኒቨርሲቲ በአንድ ወቅት ተምረናል።አንድ ዶርምም ኖረናል ስለዚህ ምን አገናኝቷቸው ገደለው ለሚለው ጥያቄ መልስ ይሰጣል።ስለዚህ ይህን ጉዳይ በዚህ እንዝጋውና ስለቀጣዩ ነገር እንወያይ።

ይልቁንስ እኔ ዛሬ የጀመርኩትን ሰማዕትነት እናንተም ቀጥሉበት ።ይህን ሰማዕትነት አላቲኖስ ብየዋለሁ።አላቲኖስ ማለት እውነት፣ከማናቸው በላይ ንጹሕ ማለት ነው ።ለቅድስት ቤት ክርስቲያን የምንከፍለው ዋጋ ንጹሕና እውነት ብቻ ይሆናል።ስለዚህ ሰማዕተ አላቲኖስን ጀመርኩት እንጅ የምትጨርሱት እናንተ ናችሁ።”ሁሉም ስለገመዳ ጽናትና ቆራጥነት ተገረሙ።

አበጋዝ  ደግሞ ‘ይህቺ ቤተክርስቲያን ዛሬም ልጅ አላት ፤ ቅዱስ ያሬድን፣ ላሊበላን፣ይምርሃነ ክርስቶስን፣አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን፣አባ ቀውጦስ፣አባ ፊሊጶስ፣አቡነ ጴጥሮስን ፣አቡነ ቴዎፍሎስን ፣መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬን፣…የሚተካ ልጅ ዛሬም ተወልዷል ።’እያለ ለራሱ ሲደሰኩር ነበር ታንቱ ንግግር የጀመረው ።

በዚህ የወረርሽኝ ሰዓት ሁሉም ሰው በተለይም ‘ክርስቲያን ነኝ’ የሚል ሁሉ ሊያነበው የሚገባ ሌላ ድንቅ መጽሐፍ ።
Stay at home till the pandemic is over
Keep calm read books with red cover
 አላቲኖስ

1 comment:

  1. DO YOU NEED A LOAN : TRUST ME WE CAN SOLVE YOUR FINANCE PROBLEM
    Do you need Personal Loan?
    Business Cash Loan?
    Unsecured Loan
    Fast and Simple Loan?
    Quick Application Process?
    Approvals within 24-72 Hours?
    No Hidden Fees Loan?
    Funding in less than 1 Week?
    Get unsecured working capital?
    Contact Us At : urbansuccessfundings@gmail.com

    LOAN SERVICES AVAILABLE INCLUDE:

    Commercial Loans.
    Personal Loans.
    Business Loans.
    Investments Loans.
    Development Loans.
    Acquisition Loans .
    Construction loans.
    Credit Card Clearance Loan
    Debt Consolidation Loan
    Business Loans And many More Loan Opportunity:

    LOAN APPLICATION FORM:
    =================
    Full Name:................
    Loan Amount Needed:.
    Purpose of loan:.......
    Loan Duration:..
    Gender:.............
    Marital status:....
    Location:..........
    Home Address:..
    City:............
    Country:......
    Phone:..........
    Mobile / Cell:....
    Occupation:......
    Monthly Income:....

    Contact Us At urbansuccessfundings@gmail.com

    Phone number : +17247693888 (Whatsapp Only)

    ReplyDelete