Saturday, November 17, 2018

.....ላንቺ....


የብዕሬ ጠብታ ላንቺ የሚመጥን ባይሆንም ቀለሙ
በሄድሽበት ሁሉ እንድታስታውሽኝ እስከ ዘላለሙ 
ፃፍልኝ ያልሽኝን ያው ተቀኘለሁልሽ
በግሩም ተፈጥሮሽ ስፍስፍ ብልልሽ
መናኝ በሚያስቱ አስማታም  ጥርሶችሽ
ቀልብን በሚያሣጡ ምትሃተኛ ዓይኖች
አንኳን ሁለት ስንኝ እንኳን ስምንት ቀለም
ህይወት ብታስከፍይ ላንቺ ብዙ አይደለም
አይመረመሬው የሠራሽ ተጠቦ
የውበት ተምሣሌት ጠይም የደም ገንቦ
የሥብዕና ጥግ የሴትነት ልኩ
ምን ብዬ ልግለፅሽ እንዴው በምን መልኩ?
ታዲያ ለዚህ ገላሽ ለዚህ ውብ ተፈጥሮ
ስምሽ ግንባሬ ላይ በደማቅ ተወቅሮ
አገልጋይሽ ልሆን አምላክ ቢፈቅድ ኖሮ
ደከመኝ ሰለቸኝ አልልም  ነበረ
ዳሩ ምን ዋጋ አለው ምኞት ሆኖ ቀረ
©/ ጌታነህ ካሴ ኅዳር 7/2011 .

No comments:

Post a Comment