Thursday, February 22, 2018

ልጆች ልከን ነበር

ልጆች ልከን ነበር ከተማ እንዲማሩ፣
ጨለማው ኑሮአችን በእውቀት እንዲያበሩ።
እነሱ እቴ ምርጦች ከሰው የተለዩ¡
እንኳን ቀለም ዘልቀው እውቀት ሊገበዩ፤ 
ያጵሎስ የጳውሎስ ብለው ሲለያዩ፣ 
የእምነት ቃላቸውን በክህደት ለውጠው፣
በብልጭልጭ ነገር በደስታ ተውጠው፣
በትምክህት በኩራት እንደተወጠሩ፣
የከፈቱትን በር ሳይዘጉት አደሩ፤
በሄዱበት መንገድ ሳይመጡበት ቀሩ።
አሁን ግን ነቅተናል ዘይደናል መላ፣
ማን ቁማር ይበላል ከእንግዲህ በኋላ?
ሴቷን በሚስትነት ለጦፈ ነጋዴ፣
ወንዱንም ማስጠበቅ ገዝቶ የበግ አዴ።
Farmed : 23/05/2010 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment