Sunday, November 19, 2017

ሐዋርያት

ኑሮን ለማሸነፍ ቤተሰብ ሊመሩ
ከላይ ታች ብለው ሲለፉ ሲጥሩ
በየሥራ መስኩ ከተሰማሩበት
መርጦ ቢጠራቸው ጌታ ለአገልግሎት
ቤትና ንብረቴን ወገኔንም ሳይሉ
ሁሉን ንቀው ትተው አምነው ተከተሉ
በዋለበት ውለው ባደረበት ሲያድሩ
ድንቅ ተዓምራቱን ማዳኑን   እያዩ፣
በሃይማኖት ጸንተው በእምነት ጠነከሩ
ምድራዊውን ትተው ለሰማዩ ኖሩ
ጣዕም ያጣውን ዓለም በቃሉ ለወጡ
እነሱ ጨው ሆነው ሁሉን አጣፈጡ
ምንጭ፦ሐመር ዘኦርቶዶሽ ተዋህዶ
            መስከረም 2009 .

No comments:

Post a Comment