Friday, November 03, 2017

እርቅ ለምኔ

አባቴን በክላሽ እናቴን በርግጫ፣
ወንድሜን በሽጉጥ እህቴን በጡጫ፣
ሲወቃ እያየሁት
ከደጃፌ ጥሎ የበቀል አውድማ፣
በሬየን ቅርጫ አርጎ ሚስቴንም ውሽማ፤
በእናቴ የወጣሁ ሴት መሆኔን አውቆ፣
በወገኖቼ ደም እጁ ተጨማልቆ፤
ህልሙ ሲሞላለት የቅዠቱ ገንቦ፣
ታረቀኝ ይለኛል ዓይኑን በጨው አጥቦ፤
ክንዴን ሳልንተራስ ሳይዝግ ምኒሽሬ፣
መቃብር ሳልወርድ እጅ እግሬን ታስሬ፤
ደመላሽነቴ ሳይታወቅ በዓለም፣
እርቀ ሰላም ብሎ ፍልስፍና የለም።
የወንድሜን ገዳይ ቅንድቡን ሳልመታ፣
የምን ድርድር ነው የምንስ ይቅርታ?

  ©ጌች ቀጭኑ

No comments:

Post a Comment