Sunday, January 22, 2017

የክርስቶስ ነገር

“የክርስቶስ ነገር እጅግ አስቸገረ። ልጅ ስለሆነ ይሆን? አንድ ጊዜ ተርቤ አላበላችሁኝም ይላል። አንድ ጊዜ አምስት እንጀራ ለአምስት ሺህ ሰው አብልቶ አትርፎ ያስነሳል። ሌላ ጊዜ ደግሞ ገንዘባችሁን እየሰበሰባችሁ ወደ ሰማይ ላኩ እዚያ ይቆያችኋልና ይለናል። ለካ የእርሱ ገንዘብ አልበቃው ቢል ወደኛ ልጁን የላከ ቀስ ብሎ ገንዘባችንን በብልሃት እንዲያከማች ኖሯል። እንግዲህ አወቅንበት ገንዘባችንንም አናባክንም። ከሰማይስ እኛ ምን አለን? ገነዘባችንን አሸክመን ወደ ዚያ ከምንልክ አንካሶችን እውሮችን ችጋረኞችን ወንድሞቻችን ይዘን እንክት እያደረግነ እንበላዋለን።በገንዛ ገንዘባችን ምን ይመጣብናል። አላመጣችሁም ብሎ የሚያደርገውን እስኪ እናያለን።”
(መጽሓፈ ጨዋታ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ) መልካም ዕለተ ሰንበት!!!

No comments:

Post a Comment