Monday, July 09, 2018

ልቤን አታድርቀው

ግድፈት የሌለበት እውነት መናገሬን ልብህ እያወቀው፣
እገሊት ከፍቷታል ያ ጎረምሳ ዝቷል በሚል እንቶ ፈንቶ ልቤን አታድርቀው።
አንተን ብሎ ትሁት ገልጋይ ደም አድራቂ፣
አንችን ብሎ ሸምጋይ ድንቄም አስታራቂ፣
ፍቅር ያሸንፋል በሚል የምፀት ቃል ከምትሳለቂ፣
ተመሳስሎ ኗሪ የቀበሮ ጃኬት ካፖርትሽን አውልቂ ።
እውነቱን ተናግረሽ ስትሄጅ ቢመሸብሽ ከዛፍ ስር እደሪ፣
ከትንሹ እግዚአብሔር ከህሌናሽ ጋራ በሰላምሽ ኑሪ።
ከራድዮን 28/10/2010 ዓ.ም

No comments:

Post a Comment